TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰላም፣ አንድነት፣ እኩልነት፣ መተባበር፣ ተስፋ፣ ፍትህ፣ ብልፅግና፣ መዋደድ፣ መቻቻል እና ይቅር ባይነት በእናት ሀገሬ ኢትዮጵያ ሰፍኖ ማየት የሁል ጊዜ ምኞቴ ነው።

ኢትዮጵያዊነት ይለምልም! ደም የፈሰሰበት አጥንት የተከሰከሰበት አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ባንዲራችን ለዘላለም ከፍ ብሎ ይውለብለብ!

ቲክቫህ ማለት ተስፋ ማለት ነው! በእናታችን ተስፋ አንቆርጥም!

#ቲክቫህ #ተስፋ #አንድነት #ሰላም #ኢትዮጵያዊነት #ፍትህ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍትህ ለብላቴናው መሀመድ!

የዛኔው ለጋ ህፃን የአሁኑ ታዳጊ መሀመድ ከዛሬ 12 አመት በፊት የ4 አመት ጨቅላ ህፃን ሳለ ነበር አፍንጫው ላይ የወጣችን አነስተኛ ስጋ ለማስነሳት ቤተሰቡ ጋር በሳኡዲ አረቢያ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል የገባው በወቅቱም እናቱ በገባበት የህክምና ክፍል አጠገብ ሁና የልጇን መውጣት ብትጠብቅም ሳይመጣ ቀረባት ከሰአታት ቡሃላም ፈፅሞ ያልጠበቀችው ያልገመተችው ዱብ እዳ ተነገራት ።

ልጇ መሀመድ በጣም ደክሞ ህይወቱ አደጋ ላይ መሆኑን ሰማች እንዴ በምን ምክንያት? ልጄ እኮ ጤነኛ ነበር ምን አደረጋችሁብኝ… እያለች ጠየቀች አለቀሰች ግን ሰሚ አላገኘችም… …

እነሆ ላለፉት 12 አመታት ወይዘሮ ሀሊማ በሞትና በህይወት መካከል የሚገኘውን ልጇን አይን አይኑን እያየች አጠገቡ ኩርምት ብላ እያለቀሰች ትገኛለች ለመሆኑ ህፃን መሀመድን ምን ቢያደርጉባት ይሆን 12 አመት ሙሉ ከገባበት ሰመመን ሳይነቃ የአልጋ ቁራኛ ያደረጉባት ይሄን ወንጀል የፈፀሙትስ አካላቶች ተጠይቀው ይሆን???

የኢትዮጲያ ኤምባሲ በሳኡዲ ለመሆኑ የመሀመድን ጉዳይ ምነው ዝም አለው??

ቢቢኤን ከወላጅ እናቱ ከወይዘሮ ሀሊማ ባደረገው አጠር ያለ ቆይታ የህፃን መሀመድ እናት ወይዘሮ ሀሊማ ይህን ብላለች...

"ወገኖቼ ሆይ ፍረዱኝ ልጄን ተቀማሁ ሀዘን ጠበሰኝ"

ሀሊማ ሁላችንም ከጎኗ ሁነን ለፍትህ እንጮህላት ዘንድ በየእምነታችን በዱአ እና ፆለት እናግዛት ዘንድ ትማፀናለች።

#ፍትህ ለብላቴናው መሀመድ

©BBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ፍትህ_ለጫልቱ!!
#JUSTICE_FOR_CHALTU!

ሴት ሰው ናት!
ሴት ሀገር ናት!
ሴትን #መድፈር ሀገርን መድፈር ነውና በሞት ይቀጡልን!

"እኛም ሴቶች ዜጋ ነን!"

መንግስት የአሲድ መድፋት ወንጀልን ያስቁምልን!

📌 #የአሲድ ጥቃት አስመልክቶ ህግ ይውጣ።
📌 #አሲድ በቀላሉ እንዳይገኝ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረግ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia