TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትግራይ

የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕረዚደንት 6 የዞን ከፍተኛ አመራሮችን ከስልጣን አነሱ።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ያነሱዋቸው ፦
- የምስራቅ 
- የደቡብ
- የማእከላይ
- የደቡብ ምስራቅ
- የሰሜናዊ ምእራብ እና  የምእራብ ዞን የህዝብ ግንኙነት ፅህፈት ሃላፊዎች ናቸው። 

ሃላፊዎቹ ከፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ በይፋ ከሃላፊነታቸው እንደተነሱ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ፅሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ በመጥቀስ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

አመራሮቹ ከስልጣን ስለተነሱበት ምክንያት የተባለ ነገር የለም።
                            
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#መክሰስTime መሆኑን እንዴት እንውቃለን? የምንወደውን ስናይ እና ስንሰማ - ከ #ሰንቺፕስ ጋር #ሰኒሞመንትስ #መክሰስTime

When do you know that it is time? Time for #SnackTime - with #SUNChips and #SunnyMoments.

Facebook: https://www.facebook.com/sunchipsethiopia
Instagram: https://instagram.com/sunchipsethiopia 
ከውጭ ሀገር ከወዳጅ ዘመድ የሚላክልዎትን ገንዘብ
በኢትዮ ዳይሬክት ቀጥታ ወደ ሂሳብዎ ያስልኩ!
EthioDirect
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
=============
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም App Store በማውረድ አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
#ድሬዳዋ

🔹" የትውልድን ስነምግባር የምትቀርጽ እና በይዞታዋም ህጋዊ የሆነችን ቤተክርስቲያን  አፍርሶ ሆቴል መስራት አግባብነት የለውም " - ቤተክርስቲያን

🔸" ቦታውን ለልማት ተፈልጎ ነው ፤ ካቢኔው የልማት ጥያቄዎችን የማስተናገድ ሃላፊነት አለበት " - የድሬዳዋ ከንቲባ ጽ/ቤት

የድሬደዋ መካነ-ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ቤተክርስቲያኗ ካለችበት ቦታ እንድትነሳ የሚል ደብዳቤ እንደላከላት አስታውቃለች።

ቤተክርስቲያኗ የከተማው አስተዳደር ውሳኔውን በ2 ቀን ውስጥ እንዲያስተካክል ጠይቃለች።

ቤተክርስቲያኗ ፤ ለ40 አመታት በስፍራው የቆየች እና ህጋዊ ይዞታ እንዳላት የገለፀች ሲሆን የድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ግን ለሆቴል ስራ በሚል በአንድ ወር ውስጥ ከቦታው እንድትነሳ ደብዳቤ መላኩን አስረድታለች።

የቤተክርስቲያኗ ዋና ሰብሳቢ ቄስ በላቸው አምባሮ ፤ " የከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት ለቤትክረስቲያኗ በላከው ደብደቤ እንዳስቀመጠው ቦታው ለሆቴል ቱሪዝም መፈለጉን የሚገልፅ ነው " ብለዋል።

ነገር ግን የትውልድን ስነምግባር የምትቀርጽ እና በይዞታዋም ህጋዊ የሆነችን ቤተክርስቲያን  አፍርሶ ሆቴል መስራት አግባብነት የሌለው እና በምዕመን መካከል ሁከትን መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

" ከዚህ በፊት ቤተክርስቲያኗ ለከተማዋ መንገድ ስራ በሚል ተባበሪ በመሆን የተወሰኑ ሜትሮችን ወደ ውስጥ ተጠግታለች " ያሉት ቄስ በላቸው፣ " ይህ ግን በህልውናዋ ላይ የመጣ ነው " ብለዋል፡፡

ስለሆነም የከተማዋ ከንቲባ ጽ/ቤት ካቢኔ የወሰነውን ውሳኔ በሁለት ቀን ውስጥ እንዲያስተካክል የጠየቁ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ቤተክርስቲያኗ ሌሎች ህጋዊ አማራጮችን እንደምትጠቀም አስገንዝበዋል።

የድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጸህፈት ቤት በበኩሉ ቤተክርስቲያኗ እንድትናሳ ካቢኔው ወስኖ ለቤተክርስቲያኗ ደብዳቤ መላኩን አረጋግጧል።

የጽ/ቤቱ  ሃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን  ፤ " ቦታው ለልማት ተፈልጎ ነው ፤ ካቢኔው የልማት ጥያቄዎችን የማስተናገድ ሃላፊነት አለበት " ብለዋል።

ነገር ግን ቤተክርስቲያኗ ጉዳዩን ተቃውማ ደብዳቤ ከመላክ ውጭ ከጽ/ቤቱ ጋር አልተነጋገረችም ያሉ ሲሆን ሁሉም ነገር የሚፈታው በንግግር ነው ብለዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮች_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት.pdf
#ትግራይ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከሰሞኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ያወጣውን ሪፖርት " ኃላፊነት የጎደለው ነው " በማለት እንደማይቀበለው አስታወቀ።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ " የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተፈናቃዮች አስመልክቶ ባወጣው ሁለተኛው ዘገባ የፌደራል መንግስት ባደረገው ጥረት በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ተጋሩ በብዛት ወደ ቄያቸው እንደተመለሱ፤ ሰብአዊ ድጋፍም እየቀረበላቸው እንደሆነ አስመስሎ ይፋዊ ዘገባ አውጥቷል " ሲል ገልጿል።

" በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጋሩ ከቄያቸው ተፈናቅለው በከፋ ሁኔታ በሚገኙበት ወቅት ፣ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ በማለት ሌተ ተቀን  ቢወተውትም የወገኖቻችን መመለስ በሚመለከት አንዳች ተግባራዊ እንቅስቃሴ ባልተደረገበት ሁኔታ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ይህን መሰል ሃላፊነት የጎደለው ዘገባ ማውጣቱ ፤ ከአሁን በፊት በትግራይ ህዝብ ላይ ሲያደርስ የነበረውን በደል የሚያስቀጥል " ነው ብሏል።

ሪፖርቱ " በትግራይ ህዝብ ስቃይ መቀለድ ነው " ያለው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ሆን ብሎ የዓለም ማህበረሰብ ለማሳሳት ያዘጋጀው ቅጥፈት ስለሆነ ተቀባይነት የለውም " ሲል ገልጿል።

የፌደራል መንግስት ይህን መሰል ሃላፊነት የጎደላቸው ዘገባዎች ሆነ ተብሎ በመዋቅሩ ሲለቀቁ የሰላም ሂደቱ የሚያውኩ ፣ መተማመን የሚያጎድሉ መሆናቸው ከግምት ውስጥ በማስገባት ተገቢ እርምጃ ወስዶ እንዲያርም ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥሪ ማቅረቡን በመቐለ የሚገኘው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከላይ ያለውን መግለጫ ካወጣው በኃላ አጭር መልዕክት በማህበራዊ ትስስር ገፁ አሰራጭቷል።

ኮሚሽኑ " በተፈናቃዮች 2ኛ ዓመታዊ ሪፖርቱ ላይ እንደተገለጸው የጂኦግራፊ ወሰኑ ትግራይን አልሸፈነም ይህም በዝግጅቱ ወቅት ተደራሽ ስላልነበረ መሆኑን እናረጋግጣለን " ብሏል። ኮሚሽኑ የተሳሳተ መረጃን ለማረም ከጊዜያዊ አስተዳደሩ (IRA) ጋር መተባበሩን እንደሚቀጥል አመልክቷል።

@tikvahethiopia
👆" የማሽላው አባት " የዓለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኢጀታ 👏

Via 👋 @TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

በማማፔይስ መተግበሪያ ቪዛ ወይም ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ገንዘብ በነፃ ወደ ኢትዮጵያ ይላኩ፡፡

የሞባይል መተግበሪያውን ከ Play Store  በማውረድ ይጠቀሙ።

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.mamapays&hl=en&gl=US

የቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ።
https://publielectoral.lat/BoAEth

#mamapays #visa #mastercard  #የሁሉም_ምርጫ