TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጨማሪ

የባህር ዳር ፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት ነዋሪዎች ምን አሉ ?

የባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዎች ከተማቸው በመከላከያ ሰራዊት ስር እንደሚገኝና ዛሬ ተኩስ እንዳልነበር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

#ባህርዳር

ነዋሪ 1

" ከትለንት ከግማሽ ለሊት በኃላ መከላከያው ተቆጣጥሮታል።

ተኩስም የለም፤ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። አንፃራዊ ሰላም አለ።

መከላከያው ነው እየተንቀሳቀሰ ያለው። ሰውም እንደ ሰሞኑን ሳይሆን መንቀሳቀስ ጀምሯል። ግን አገልግሎት መስጫ ተቋማት ዝግ ናቸው በተረፈ ቁስለኛ እየተነሳ ሃኪም ቤት እየሄደ ነው ፣ የሞተውም እየተቀበረ ነው።

ዘንዘልማ አካባቢ ብዙ ሰው ስለሞት እነሱ እየተነሱ እየተቀበሩ ነው። ከሟቾች ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ የተወሰኑ ናቸው እንጂ በቤተሰብ አማካኝነት እዛው እየተቀበረ ነው። ብዛት ያለው ሰው ደግሞ ከመኮድ ይወረወር የነበረ ከባድ ተወዋሪ መሳሪያ እሱ ነው ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰው። መኖሪያ ቤት ላይ እየወደቀ፤ ህፃናቶችም ሞተዋል።

ቁጥሩን ባልገልፅም ብዙ ሰላማዊ ሰው ሞቷል፣ በተለይ ቀበሌ 14 ላይ ከፍተኛ ውጊያ ነበር፤ በጣም ብዙ ሰው ሞቷል። ዛሬ ብዛት ያለው ሰው ቀብር ነው የዋለው። ህዝቡ እየወጣ መቅበር ጀምሯል። "

ነዋሪ 2

" እኛ ኤርፖርት አካባቢ ነን። ዛሬ ሰላም ነው። ተኩስም የለም። የተረጋጋ ነው። ግን ብዙ ሰው ፍራቻ ስላለው ወደ ከተማ አይሄድም። በጣም ብዙ የሞተ ሰው ስላለ ፍራቻ አለ። ነገር ግን ከንጋት ጀምሮ ምንም ድምፅ የለም።

በአብዛኛው ሲቪልያን ነው የሚሞቱት ካለመሳሪያ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ፣ የሚታኮሱት አይደለም የሚሞቱት በብዛት። ጀሌው አለ አይደል በአጋጣሚ መንገድ ለመዝጋት የሚሄደው ነው። "

#ጎንደር

ነዋሪ 1

" ጎነደር ከትላንት ማታ ጀምሮ ማለት ይቻላል ተኩሱ ቆሟል። መከላከያው ከተማው ውስጥ ያሉትን መንገዶች የማፅዳት ስራ እየሰራ ነው ያለው። መንገዶች በድንጋይም፣ በእንጨትም ተዘጋግተው ስለነበር።

ሌሎች እንቅስቃሴዎች ገና ናቸው። የሰው እንቅስቃሴም የለም። ቤት ውሥጥ ቁጭ ብለን ነው የሰነበትን ዛሬ ሳምንታችን ነው። የሚቀጥለው ምን እንደሚሆን እየጠበቅን ነው።

በትክክል ስለደረሰው ጉዳት ይህ ነው ማለት ባልችልም፤ ሰው ግን ለሳምንት ከገበያ ከሌሎችም አገልግሎቶች ተገልሎ መቆየቱ ብዙ ሰው አላሰበውም እሮብ ማታ ድረስ ጤናማ ስራውን እየሰራ ከዚያ ምሽት በኃላ ግን መውጣት መግባት  የማይቻልበት፣ የጥይት ድምፅ የከባድ መሳሪያ ሲስተናገድ ነበር ወደ ህክምና ለመሄድም ትራንስፖርት የለም ጉዳቱ ቀላል አይሆንም። "

ነዋሪ 2

" ዛሬ ተኩስ የለም። ከተማ ውስጥ ምንም እንቅስቃሴ የለም። ከመከላከያ ውጭ የሚንቀሳቀስ የለም። ሰው ከቤት አልወጣም።

ሰላማዊ ሰዎች ብዙ ተጎድተዋል።

ህክምና ለማግኘትም አልተቻለም። ጉዳቱ ከመብዛቱ አንፃር እንዲሁም አንስቶ የሚወስድም አልተገኘም።

የሞቱ ሰዎች ትላንት አልፎ አልፎ ተቀብረዋል። ከሟች ብዛት አንፃር ያልተቀበሩ አሉ። "

በተመሳሳይ በሸዋሮቢት ከተማ ሀገር መከላከያ የገባ ሲሆን ዛሬ የተረጋጋ ሁኔታ መኖሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በግጭቱ ሳቢያ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ የሞቱ ሰዎች እየተለቀሙ ተቀብረዋል።

አንድ ነዋሪ እሳቸው ብቻ ባረጋገጡት 13 ንፁሃን እንደሞቱ ገልፀው ሚካኤል ቤተክርስቲያን 10 ሰው፣ ማርያም 2 ሰው፣ ሙስሊም መቃብር 1 ሰው መቀበሩን መረጃ እንዳላቸው ተናግረዋል። በየገጠሩ ያለው ገና አልታወቀም ሲሉ አክለዋል።

ትራንስፖርት አለመኖሩ፣ መንቀሳቀስም አስፈሪ ስለነበር ተጎጂዎችን ወደሆስፒታል ለመውሰድ አስቸጋሪ እንደነበር ነዋሪዎች ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ቻይና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ቻይና አቅንተው በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ናቸው። ከጠ/ሚ ፅ/ቤት በወጣ መረጃ የቻይናው ጠ/ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በኃላም የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከሪያ መንገዶች ላይ መክረዋል ተብሏል። ከሁለትዮሽ…
#UPDATE

ቻይና የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር በመሆን ከቻይናው ፕሬዝደንት ሺ ጂንፒንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

ፕሬዝዳንት ሺ ፤ በኢትዮጵያ #ብሪክስን መቀላቀል ሁነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩን " እንኳን ደስ ያለዎ " ብለዋቸዋል።

የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነትም ከሁሉን አቀፍ ፅኑ ግንኙነት ወደ ሁኔታ የማይፈታው ስልታዊ ትብብር እና ወዳጅነት (All Weather Strategic Cooperation Partnership) ደረጃ ከፍ ማለቱን በይፋ አብስረዋል።

ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አድንቀው ከቻይናው አረንጓዴ ልማት ፖሊሲ ጋር ተናባቢ በመሆኑ የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋግጠዋል ተብሏል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ፤ የቻይና ኢንቬስትመንት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እመርታ የሚኖረውን አስተዋፅዖ ያነሱ ሲሆን በተለይም በ5ቱ ቁልፍ ምሰሶዎች፦
- በግብርና
- ማኑፋክቸሪንግ
- አይሲቲ
- ማእድን ልማት እና ቱሪዝም #ተጨማሪ ኢንቬስትመንት እንዲኖር የማበረታቻ ጥሪ ማቅረባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ?

በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።

አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።

ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።

በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።

ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።

በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።

ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።

ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።

የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።

በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።

ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።

የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል  ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።

#ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል። ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ…
#ተጨማሪ #ብሔራዊ_ፈተና

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኦንላይን ከሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጋር በተያያዘ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አናግሯል።

አመራሩ ፥ " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።

በየማህበራዊ ሚዲያው " የኦንላይን ፈተና ቀርቷል ፤ ሁሉም ተፈታኝ ፈተናውን በወረቀት ይወስዳል " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም ሀሰተኛ መረጃ እንደሆነም አረጋግጠዋል።

ተማሪዎች በሀሰተኛ መረጃ ሳይረበሹ ለፈተናው ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት  ፥ የ2016 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በኦንላንይ እና በወረቀት እንደሚሰጥ አረጋግጧል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ  ሃሰተኛ ነው ብሏል።

ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እንዲሁም በኦንላይን እንደሚሰጥ አሳውቋል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia