TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

#ቅዱስ_ገብርኤል

የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ቅዱስ ገብርኤል) በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።

በዓሉን በደማቅ መልኩ ለማክበር የገዳሙ አስተዳደር ጽ/ቤት ከፀጥታ አካላት ከአከባቢው ምዕመናን ጋር ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ምእመናን ለበዓሉ ሲመጡ መታወቂያ ከእጃቸው ላይ እንዳይለይ መሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#ቅዱስ_ገብርኤል

• " ምንም የጸጥታ ስጋት አይኖርም " - የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ

• " የሀዋሳ ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ ነው ያለው " - የሀዋሳ ፖሊስ መምሪያ

ነገ የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ እና የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አሳውቀዋል።

በዓሉ በተለይ በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ በርካታ እንግዶች የሚታደሙበት እንደመሆኑ ያለምንም የጸጥታ ስጋት እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው እንደ ክልል በቂ ዝግጅት በመደረጉ ምንም የጸጥታ ስጋት አይኖርም ብሏል።

የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ በበኩኑ የቅዱስ ገብርኤል በዓል በከፍተኛ ድምቀት በሚከበርባት ሀዋሳ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ዝግጅት ተጠናቋል ሲል አሳውቋል።

የከተማው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ መሆኑንም አረጋግጧል።

በአሁኑ ወቅት ኅብረተሰቡ አካባቢውን በመጠበቅ እና መረጃ በመለዋወጥ ትልቅ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

ከዚህ በተጨናሪ በጠ/ሚኒ ዐቢይ አሕመድ ጥሪ ከውጭ አገራት የሚመጡትን እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መደረጉን ሀዋሳ ፖሊስ አሳውቋል።

የእንግዶችን ሰላም ለማስጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች አስተማማኝ ዝግጅት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንግዶች ምንም ዓይነት የጸጥታ ስጋት ሊኖራቸው አይገባም ተብሏል።

ነጋዴዎች በተለይ ሆቴሎች አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ ጠንካራ ቁጥጥር እንደሚደረግ እና የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለእንግዶች መኪና ማቆሚያ እንደተዘጋጀ የሀዋሳ ፖሊስ አሳውቋል።

#Kulubi #Hawassa #EPA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

#ቅዱስ_ገብርኤል

የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ቅዱስ ገብርኤል) በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።

በዓሉን በደማቅ መልኩ ለማክበር የገዳሙ አስተዳደር ጽ/ቤት ከፀጥታ አካላት ከአከባቢው ምዕመናን ጋር ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ፅ/ቤቱ የፓርኪንግ ችግር ፈፅሞ እንጋይገጥም አዲሱ የቤተመንግስት ፓርኪንግ መፈቀዱንም አመልክቷል።

ምእመናን ለበዓሉ ሲመጡ መታወቂያ ከእጃቸው ላይ እንዳይለይ መሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopia