TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወንድሙ #የተገደለበት ሁሉ የገዳዮቹን ወንድሞች #ልግደል ካለ ሁላችንም ያለ ወንድም እንቀራለን!!
.
.
.

"በክልላችን በነበረው ብልሹ አስተዳደር ብዙ ችግሮች ተፈጥረዋል። ሁላችንም ተበድለናል። የተፈጸሙትን በደሎችና ችግሮች እንቁጠራቸው ብንል አንችልም። ይቅርታ አድርጉልኝና ማን ማንን እንደሚያጽናና አላውቅም። በደሎቹን ማስታወስና ቁስላችንን መቆስቆስ አያስፈልግም። አልሃምዱሊላህ አሁን ሁሉም አልፏል። ወገኖቼ እምባ ይብቃን፥ ማቃችንን እንጣል፥ በአዲስ መንፈስ እንነሳ። የጥላቻን እና ብቀላን ጦስ እስኪበቃን አይተናል። ወንድሙ የተገደለበት ሁሉ የገዳዮቹን ወንድሞች ልግደል ካለ ሁላችንም ያለ ወንድም እንቀራለን፥ ሁላችንም እንጠፋለን። ጥላቻ #በፍቅር እንጂ በበቀል አይሸነፍም። ስለዚህ #ካለፈው ተምረን #በፍቅር እና #በይቅርታ፥ በአዲስ ሞራል እጅ ለእጅ ተያይዘን ለጋራ ሰላም፥ ዲሞክራሲና ልማት እንረባረብ"

የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር (#ሙስጠፈ_መሀመድ_ኡመር)

©Yoseph Legess
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጳጉሜ 2 - የፍቅር ቀን

#በፍቅር ተደምረን፤ #በይቅርታ እንሻገር!

ክፉ አያግኛችሁ! ሰላም እደሩልኝ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለልጆቻችን ስንል የአያቶቻችንን መጥፎ ታሪክ #በይቅርታ እንዝጋው!

አዲሲቷ ኢትዮጵያ እኔ ነኝ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
* Confirmed በደቡብ አፍሪካ በነበረው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ድርድር ላይ ከብዙ ክርክሮች በኃላ በሁለቱም ወገኖች የተፈረመው የስምምነት ዝርዝር ሰነድ ከላይ የተያያዘው ነው። በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ስምምነቱ ከተፈረመ በኃላ የተለያዩ ስምምነቱን የሚገልፁ " Draft " ወረቀቶች ሲሰራጭ የነበር ቢሆንም ከሰላም ንግግሩ አመቻቾች (አፍሪካ ህብረት)፣ ከሰላም ንግግሩ ተሳታፊዎች…
የ ' ሰላም ስምምነቱ ' #ስኬታማ እንዲሆን ምን ይደረግ ?

የፕሪቶሪያው የ "ሰላም ስምምነት" ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ስምምነት የተደረሰባቸው ነጥቦች በአግባቡ መሬት ይዘው፤ ሲፈጸሙና የጦርነቱ ሰለባ የሆነው ሕዝብ እፎይታን ሲያገኝ እና ሲታከም ብቻ መሆኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በላከል መግለጫ አሳውቋል።

ም/ ቤቱ የሰላም ስምምነቱ ፍሬያማ ይሆን ዘንድ ፦

- የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሓት በስምምነቱ ማእቀፍ ሊተገብሩ በተስማሙት ሠነድ መሠረት ፦ የአፈጻጸም ሂደቱ አካታች ፣ ተዓማኒ እና ግልጽ ሆኖ በታመለት ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ እንዲቻል በፍጹም ቁርጠኛነት እንዲሁም በተጠያቂነት መንፈስ እንዲያከናውኑ በአጽንዖት ጠይቋል።

- የፓለቲካ ኃይሎች ስምምነቱ ፍሬ እንዲያፈራና በሀገራችን ዘላቂ ልማትና እድገት እንዲኖር የሰላም ደጋፊ ሊሆኑ ይገባል ብሏል። የእልህ እና የብሽሽቅ ፕሮፖጋንዳዎች ቆመው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ኋላቀር አስተሳሰብ ሊወገዝ እንደሚገባው ገልጾ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን #በይቅርታ ሕመማችንን በጋራ እንድናክም ሲል ጥሪ አቅርቧል።

- የተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት እጅግ በጣም ውጤታማ ይሆን ዘንድ በጦርነቱ ሳቢያ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብሏል ፤ ለዚህም ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርቧል።

- በተደረገው የሰላም ስምምነት ስኬታማነት ላይ ስጋት ያላቸው ዜጎች ፣ ፖለቲከኞች ፣ አክቲቪስቶች ፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሌሎችም ኢትዮጵያ ከሰላም ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌላት በማወቅ ስለሰላም መልካሙን እንዲያስቡና እንዲያደርጉ አሳስቧል።

(ሙሉ የም/ቤቱ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በትግራይ ክልል የሚገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ልዑካን ቡድን አባላት ዛሬ ከሰዓት በጦርነት ምክንያት ጉዳት የደረሰበትን ታሪካዊውን የ " አል ነጃሺ መስጂድ "ን ጎብኝተዋል። የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ አደም ፤ " ነጃሺ ያለ ኢትዮጵያ ሙስሊም ምንም ነው፤ የሚለማው ታሪኩም የኢትዮጵያ ሙስሊም ነው " ብለዋል። የፌዴራል መጅሊሱ…
#Update

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና የትግራይ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በመካከል የነበራቸውን ችግር #በይቅርታ ከፈቱ በኃላ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት መልሰዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮችም ወደ ትግራይ ተጉዘው በጦርነት የተጎዳውን የአልነጃሺ መስጂድን ጉብኝተው በጦርነት ተፈናቅለው መጠለያ ውስጥ ላሉ  እና በድርቅ ለተጎዳው ህዝብ ድጋፍ ሰጥተው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።

የተደረገው ድጋፍ የጥሬ ገንዘብ፣ የመድሃኒትና የእህል ሲሆን የርክክብ ስነ-ሰርዓቱ ዛሬ በመቐለ ከተማ ተከናውነዋል።

ድጋፉ በዝርዝር ምን ይመስላል ?

1ኛ. እህል 5,700 ኩንታል በቆሎ/እህል ብር 24 ሚልዮን የሚያወጣ።

2ኛ. መድሐኒት 1 ኮንተይነር 40 ፊት መድሐኒት ብር 40,200,000 ብር የሚያወጣ።

3ኛ. ለአልነጃሺ ትራንስፎርመር  3 ሚልዮን ብር

4ኛ. ለሌሎች 1.2 ሚልዮን ብር

ጠቅላላ ብር 67 ነጥብ 2 ሚልዮን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለትግራይ ህዝብ መደረጉ ተነግሯል።

መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።

ፎቶ፦ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
               
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የፖሊስን የምርመራ…
#FederalPolice

የፌዴራል ፖሊስ " በሽብር እና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ " ብሎ በቁጥጥር ካዋላቸው መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከ1989 ዓ ም ጀምሮ እሰከ 1999 ዓ ም በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም 3 ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት  2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 1999 ዓ.ም በዋለው ችሎት ፦
- በዘረፋ፣
- በቅሚያ፣
- በሌብነት፣
- በቤት ሰብሮ  ስርቆት እና በደንብ መተላለፍ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበት ነበር።

ተጠርጣሪው ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ ፣ ጀማል ኑሩ እና ዳዊት ድሪባ በዳኔ የሚሉ ስሞችን በመጠቀም ፦

➡️ 11 ጦር መሣሪያ መዝረፍ ወንጀል፣

➡️ 6 ቅምያ ወንጀል፣

➡️ 3 ሌብነት ወንጀሎች፣

➡️ 3 ሰው #መግደል ወንጀል፣

➡️ 2 ስርቆትና ቤት ሰብሮ ስርቆት ወንጀሎች፣

➡️ አንድ ሐሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል፣

➡️ ከእስር ማምለጥ ወንጀል

➡️ አንድ ደንብ መተላለፍ የወንጀል ሪከርድ በአጠቃላይ 28 የወንጀል ሪካርዶች እንዳሉበት ፖሊስ አመልክቷል።

ከዚህ ውስጥ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት መጋቢት 24 ቀን በዋለው ችሎት ስድስት መዝገቦችን ሦስት ጊዜ አጣምሮ  ሦስት ጊዜ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ ተላልፎበት ነበር።

እንደገና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ሚያዚያ 30 ቀን 2000 ዓ.ም በዋለው ችሎት በጦር መሣሪያ የታገዘ የዘረፋ፣ ከአስር ቤት የማምለጥና በሌብነት ወንጀል የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጠት አስተላልፎበት ነበር።

ተጠርጣሪው በውሳኔው መሠረት ማረሚያ ቤት የገባው ይግባኝ ጠይቆ ሞት ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ የተቀየረለት ቢሆንም በድጋሚ ይግባኝ በማለቱ ቅጣቱ ወደ 25 ዓመት ተቀንሶለት ለ17 ዓመታት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ #በይቅርታ መፈታቱን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር ማረጋገጥ እንደተቻለ ተገልጿል።

#EthiopianFederalPolice

@tikvahethiopia