TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Russia የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዙ፡፡ ፑቲን ከገቡበት የዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከምዕራባውያን ሃገራት ጋር ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ጦሩ በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንዲሆን ያዘዙት፡፡ ዛሬ ከከፍተኛ ባለስልጣናቶቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል የሆኑ…
#WW3

" ምዕራባውያን ሩስያን ወደ 3ኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ ነው " - የቤላሩስ ፕሬዜዳንት

የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ የምዕራባውያን ማዕቀቦችን " ሩሲያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ " ነው ሲሉ ተጠያቂ አድርገዋል።

#NATO ሀገራት ሩስያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንት ሉካሼንኮ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዝዳንቱ ምዕራባውያን ከማዕቀብ ጋር በተያያዘ እየሄዱበት ያለው መንገድ ከጦርነትም የከፋ ነው ያሉ ሲሆን ይህ ደግሞ ሩሲያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፋ ነው ብለዋል።

ምዕራባውያን ከጽንፈኛ እርምጃዎቻቸው ወደኃላ ማለት ካልጀመሩ መጨረሻው ወደ #ኑክሌር_ግጭት ሊያመራ እንደሚችል ፕሬዜዳንቱ አስጠንቅቀዋል።

ይህ የቤላሩስ ፕሬዝዳንት ማስጠንቀቂያ የተሰማው የሩስያ አቻቸው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው #በከፍተኛ_ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን ካዘዙ በኃላ ነው።

@tikvahethiopia