TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update

ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ በዩክሬን የምታካሂደውን ወታደራዊ ኦፕሬሽን #ወዲያው እንደምታቆም አስታወቀች።

ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ፦

1ኛ. ወታደራዊ እርምጃ እንድታቆም።

2ኛ. ገለልተኛ አቋም እንድትይዝ ህገመንግስቷን እንድትቀይር (እንደ #NATO አይነት ጥምረት ውስጥ እንዳትገባ እንድታረጋግጥ)

3ኛ. ክሬሚያን እንደ ሩሲያ ግዛት እንድትቀበል።

4ኛ. የዶንቴስክ ​​እና የሉሀንስክ ተገንጣይ ሪፐብሊኮችን እንደ ነፃ ሀገር እንድትቀበል የሚሉት ናቸው።

እነዚህ ከተሟሉ ሩስያ ዩክሬን ውስጥ ምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ ወዲያውኑ እንደምታቆም ገልፃለች።

የክሬምሊን ቃልአቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በስልክ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ ዩክሬን ቅድመ ሁኔታዎቹን እንደምታውቅ እና ተፈፃሚ የሚሆኑ ከሆነ የወታደራዊ ዘመቻው ወዲያውኑ እንደሚቆም እንደተነገራት ገልፀዋል።

ከዩክሬን ወገን በኩል ወዲያው የተሰጠ ምላሽ የለም።

በሌላ በኩል ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሶስተኛው ዙር ድርድር ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia