TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአቶ #ጌታቸው_አሰፋ ጉዳይ፡ ፖለቲካዊ ወይስ ሕጋዊ መፍትሄ?
.
.

የትግራይ ክልል አሳልፌ #አልሰጥም ቢል በቀጣይ ምን ሊከሰት ይችላል?

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ አቶ ጌታቸውን ለመያዝ ሰው #መግደል የለብንም ማለታቸው ይታወሳል። አቶ #አብረሃም አቶ ጌታቸውን ለመያዝ የኃይል እርምጃ ሊወሰድ እንደማይገባ ይናገራሉ።

"አንድን ሰው ለመያዝ ተብሎ ወደ ጦርነት ይገባሉ ብዬ አላስብም የፌደራል መንግሥትም ፖለቲካውን ለማስተካከል ሲል ዝምታን ይመርጣል ፤ የትግራይ ክልልም የራሱን ህዝብ የራሱን ደህንነት ይጠብቃል ብየ አስባለሁ።" ይላሉ።


https://telegra.ph/የአቶ-ጌታቸው-አሰፋ-ጉዳይ-ፖለቲካዊ-ወይስ-ሕጋዊ-መፍትሄ-01-07
ወንጀል ነክ መረጃ‼️

በሞያሌ ከተማ በጦር መሳሪያ በመታገዝ ከባድ የሰው #መግደል ሙከራና ግድያ የፈፀሙ ግለሰቦች ላይ ዐቃቤ ሕግ ክስ መሰረተ።

1ኛ ተከሳሽ ወታደር ማትያስ ሞጉሬ እና ሌሎች 5 ተከሳሾች በወንጅል ሕጉ አንቀጽ 27(1)፣32(1)(ለ) እና 539 (1) (ሀ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ ሰውን ለመግደል በማሰብ መጋቢት 01 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት ሲሆን በሞያሌ ከተማ ልዩ ቦታው ሸዋ በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በክስ መዝገቡ የተጠቀሰው 3ኛ ተከሳሽ ኮ/ል አብርሃ አረጋይ ማንኛውንም ጸጉረ ልውጥ ሰዎችን ተኩስ እና ግድሉ በማለት፣ ለ2ኛ ተከሳሽ አስር አለቃ ሀብታሙ ተገኝ፣ ለ4ኛ ተከሳሽ ወታደርር አብዱልፈታህ ዱቦ ለ5ኛ ተከሳሽ አስር አለቃ ስለሺ ሽናሞ እና ለ6ኛ ተከሳሽ አስር አለቃ አስደናቂ ወረና ትዕዛዝ በመስጠት ተከሳሾች በተለያዩ ሰዎች ላይ በክላሽ ጠመንጃ ጥይት በመተኮስ የአካል ጉዳት፣ የግድያ ሙከራና የግድያ ወንጅል በመፈፀማቸው በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁ ድንበር ተሻጋሪ እና አገራዊ ጉዳት የሚያስከትሉ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ የካቲት 28 ቀን 2011ዓ.ም በአንድ መዝገብ በ6ቱ ተከሳሾች ላይ 15 ክስችን መስርቷል፡፡

ተከሳሾች በመከላከያ እስር ቤት ለ 9ወራት በምርመራ ላይ ቆይተው ከወርሃ ጥቅምት2011 ዓ.ም ጀምሮ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቆይተዋል፡፡

አቃቤ ህግም በ1ኛ ተከሳሽ ላይ በሁለት የግድያ ሙከራና በአንድ ከባድ ግድያ፣ በሁለተኛ ተከሳሽ ላይ በ3 ከባድ ግድያ በ1 ከባድ የግድያ ሙከራ፣ በሶስተኛ ተከሳሽ ላይ በ4 ከባድ የግድያ ሙከራ በ6 ከባድ ግድያዎች በ4 ተከሳሽ በአንድ ከባድ ግድያ በአንድ ከባድ ግድያ ሙከራ በ5 ተከሳሽ በ2 ከባድ የግድያ ሙከራና በ3 ከባድ ግድያ በ6 ተከሳሽ ላይ በአንድ ከባድ የግድያ ሙከራና በአንድ ከባድ ግድያ አቃቤ ሀግ ክስ መስርቶባቸዋል፡፡

ተከሳሾች #ተከላካይ_ጠበቃ በግላቸው ማቆም እንደማይችሉና መንግስት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው ለፍርድቤቱ የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ ፍርድቤቱም መንግስት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው ፈቅዶ ለመጋቢት 5 ቀን 2011 ዓ.ም የክስ ሂደቱን ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የፖሊስን የምርመራ…
#FederalPolice

የፌዴራል ፖሊስ " በሽብር እና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ " ብሎ በቁጥጥር ካዋላቸው መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከ1989 ዓ ም ጀምሮ እሰከ 1999 ዓ ም በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም 3 ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት  2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 1999 ዓ.ም በዋለው ችሎት ፦
- በዘረፋ፣
- በቅሚያ፣
- በሌብነት፣
- በቤት ሰብሮ  ስርቆት እና በደንብ መተላለፍ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበት ነበር።

ተጠርጣሪው ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ ፣ ጀማል ኑሩ እና ዳዊት ድሪባ በዳኔ የሚሉ ስሞችን በመጠቀም ፦

➡️ 11 ጦር መሣሪያ መዝረፍ ወንጀል፣

➡️ 6 ቅምያ ወንጀል፣

➡️ 3 ሌብነት ወንጀሎች፣

➡️ 3 ሰው #መግደል ወንጀል፣

➡️ 2 ስርቆትና ቤት ሰብሮ ስርቆት ወንጀሎች፣

➡️ አንድ ሐሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል፣

➡️ ከእስር ማምለጥ ወንጀል

➡️ አንድ ደንብ መተላለፍ የወንጀል ሪከርድ በአጠቃላይ 28 የወንጀል ሪካርዶች እንዳሉበት ፖሊስ አመልክቷል።

ከዚህ ውስጥ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት መጋቢት 24 ቀን በዋለው ችሎት ስድስት መዝገቦችን ሦስት ጊዜ አጣምሮ  ሦስት ጊዜ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ ተላልፎበት ነበር።

እንደገና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ሚያዚያ 30 ቀን 2000 ዓ.ም በዋለው ችሎት በጦር መሣሪያ የታገዘ የዘረፋ፣ ከአስር ቤት የማምለጥና በሌብነት ወንጀል የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጠት አስተላልፎበት ነበር።

ተጠርጣሪው በውሳኔው መሠረት ማረሚያ ቤት የገባው ይግባኝ ጠይቆ ሞት ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ የተቀየረለት ቢሆንም በድጋሚ ይግባኝ በማለቱ ቅጣቱ ወደ 25 ዓመት ተቀንሶለት ለ17 ዓመታት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ #በይቅርታ መፈታቱን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር ማረጋገጥ እንደተቻለ ተገልጿል።

#EthiopianFederalPolice

@tikvahethiopia