TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አዲስአበባ #መታወቂያ

“ በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን ” - CRRSA

ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው አዲስ አበባ ከተማ ለመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት በቅርብ ጊዜ መሰጠት ይጀመራል ተብሎ ነበር።

ነገር ግን እስካሁን አገልግሎቱ አልጀመረም።

ነዋሪዎችም መቼ እንደሚጀምር ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቼ ነው አገልግሎቱ መስጠት የሚጀምረው ? ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮናስ አለማየሁን ጠይቋል።

እሳቸውም በሰጡት ምላሽ፣ “ በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን ” ብለዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው በዝርዝር ምን አሉ ?

➡️ ከመሸኛ ጋር ተያይዞ ፣ ከክፍለ አገር ለሚመጡ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎቱ #ዝግ አይደለም።

- በሕመም፣
- በትምህርት እድል፣
- ተጋቢዎች ሆነው ከሌላ ቦታ ሲመጡ እዚህ (አ/አ) አንዱ ተጋቢ ካለና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ከሆነ፣
- በሥራ ዝውውር ከሆነ እነዚህ ሁሉ አልተከለከሉም። የተፈቀዱ አገልግሎቶች ናቸው።

➡️ የተከለከለው፣ ያለ ምክንያት ዝም ብሎ ለሚመጣ ነዋሪ ነው። ያለ ምክንያት ስንል በእርግጥ በምክንያት የሚመጣ አለ። ግን አዲስ አበባ ውስጥ ያለውን አጠቃላይ ነዋሪ አገልግሎት ቁጥጥር ለማበጀት የተደረገ ነው።
 
ኃላፊው በሰጡት ቃል ፥ " መሸኛ አስገብተው መረጃዎችን እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቀናል " ብለዋል።

በጣም ባጠረ ጊዜ እንደሚጀመር አመልክተዋል።

" የገጠመን አንዱ ትልቅ ፈተና የነበረው (ለ15 ቀናት አካባቢ) አዲስ መዝጋቢ መመዝገብ ከባድ ሆኖብን ነበር፣ ቴክኒካል ችግር ተከስቶ። እሱን ፈትተናል " ያሉት አቶ ዮናስ " በዚህ ምክንያት አዲስ ተመዝጋቢ የሆኑ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የነበሩ ተገልጋዮች ቁጥራቸው ከፍ (አገልግሉቱን በመቋረጡ) ስላለ እሱን ማቅለል ስላለብን ነው። እሱን እንዳቀለልን እንጀምራለን " ሲሉ አስረድተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ዛሬ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ ' ከፖሊስ ስራ ' ጋር በተያያዘ ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ፕሮግራም አለ።

ይህ ተከትሎ መንገዶች ተዘግተዋል።

የተዘጉት መንገዶች ፦
- ከልደታ በላይኛው መንገድ  ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከአፍሪካ ህብረት  ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከጠማማ ፎቅ  በንግድ ምክር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከገነት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከሰንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከቡናና ሻይ በላይኛው መንገድ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ሲሆኑ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ነው የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳወቀው።

በመሆኑም ፦
° በስራ ላይ ምትገኙ አገልግሎት የምትሰጡ አሽከርካሪዎች ፣
° ወደ ስራ እየገባችሁ ያላችሁ ሰራተኞች
° ከስራ ወጥታችሁ ወደ የቤታችሁ እየሄዳችሁ ያላችሁ ነዋሪዎች ይህን መረጃ ተመልክታችሁ አማራጭ መንገድ ተጠቀሙ።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ ከተማ የወጣው የመሬት ሊዝ  ጨረታ ተራዘመ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክፍለ ከተማ  ፤ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ በሌሎችም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ለማስተላለፍ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል። በዚህም ከሚያዚያ 10 ቀን 2016…
#አዲስአበባ #ሊዝ

የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል።

• በአንድ ካሬ ሜትር አሸናፊ የሆነው ከፍተኛ ዋጋ 470 ሺህ ብር ሲሆን ዝቅተኛ 20 ሺህ 100 ብር ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የ2ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ ተሰራጭቷል።

በጨረታው ዝቅተኛ ዋጋ የተመዘገበው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ሲሆን ይህም በካሬ ሜትር 20 ሺህ 100 ብር ነው።

ከፍተኛው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካሬ ሜትር 470 ሺህ ብር እንደሆነ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በካሬ ሜትር 470 ሺህ ብር ያቀረበው " ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ት/ቤት " መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአሸናፊዎች ዝርዝር ላይ ተመልክቷል።

በአጠቃላይ 4 ሺህ 201 ተጫራቾች የጨረታ ሰንድ በኦንላን መግዛታቸው ተነግሯል። ከነዚህ ውስጥ 2 ሺ 972 ሰነዶች ተሟልተው ተመላሽ እንደተደረጉ ተገልጿል።

1ኛ የወጡ አሸናፊ ተጫራቾች በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ለም ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ኤም.ኤ ህንጻ  ላይ የአዲስ አበባ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በመቅረብ የሊዝ ውል እንዲፈጽሙ ጥሪ ቀርቧል።

1ኛ የወጡ ተጫራቾች ውል የማይፈጽሙ ከሆነ ዕድሉ 2ኛ ለወጡት ተጫራቾች ተላልፎ ይሰጣል።

@tikvahethiopia
#ሪልስቴት #አዲስአበባ

° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች

° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ የገቡበት ቤት፦
- ውሃ፣
- መብራት፣
- ጀነሬተር
- የውሃ ታንከር የሚባሉ መሠረት ልማቶች እንደሌሉ ገልጸዋል።

ቤት ገዢዎቹ ከዚህ ቀደም፣ “ ቅሬታ ባቀረብንበት ወቅት የኖህ ጠበቃ በ1 ወር ከ 15 ቀን ጊዜ ውስጥ የጋራ መሠረተ ልማቶች አጠናቀው እንደሚያስረክቡ ቃል ተገብቶልን ነበር ” ሲሉ አስታውቀዋል።

“ እስካሁን እንኳን ሊጨርሱ ምንም እንቅስቃሴ የለም ” ብለው፣ “ ቤት ውስጥ የገቡ ቤት ገዢዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል። መብራት የለም፣ ውሃ የለም፣ ውሃ ታንከር የለም ” በማለት አማረዋል።

“ እነዚህ መሰረተ ልማቶችን ውላችን ላይ አሟልተው እንደሚሰጡን ተስማምተን ነው ቤቱን የገዛነው። ኖህ ውሉን ጥሷል ” ነው ያሉት።

“ ይባስ ብሎ ቤት ገዢ #የቤት_ክራይ_ሽሽት ወደገዛው ቤቱ መሰረታዊ ነገር ባልተሟላበት ሁኔታ ለመግባት ተገዶ መብራት በሳይቱ ዙርያ ካሉ ቤቶች በህገወጥ መንገድ ለመቀጠል ተገዷል ” ሲሉ አክለዋል።

“ ግቢው በተጠላለፈ የኤሌትሪክ ገመድ በገመድ ሆኗል ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ “ ይህ ለሚኖሩት ሰዎችም ሆነ ለልጆቻቸው ትልቅ አደጋ ይፈጥራል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ሁነቱን የሚያሳይ ቪዲዮም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ልከዋል።

በጠበቃቸው በኩል ኖህ ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ምላሽ እንዳልሰጣቸው አስረድተው " የመፍትሄ ያለህ " ብለዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት ጠበቃቸው ለኖህ ሪልስቴት የጻፈው ደብዳቤ ፥ ኖህ የቤቶቹን መሠረተ ልማት እያሟላ እንዳልሆነ፣ ምላሽ እንዲሰጥ ቢጠይቅም ምላሽ እንዳልሰጠ ያትታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ላነሷቸው እያንዳንዱ የቅሬታ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ ኖህ ሪልስቴትን ጠይቋል።

የድርጅቱ የሕግ አማካሪ እና ጠበቃ አቶ ዮሴፍ ደስታ በሰጡት ቃል፣ “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” ብለዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-10

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።

የ1445ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል።

የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅም ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

የሶላት ስነስርዓቱ የሚካሄደው በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ነው።

ይህ ተከትሎ ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የሶላት ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

በዚህም መሰረት ፦

- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ

- ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ

- ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

- ከብሔራዊ ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ

- ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ

- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ

- ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን መገንጠያ ላይ

- ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ

- ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ነገ ለስራ ይሁን ዘመድ ጥየቃ ወይም ደግሞ ለተለያየ ፕሮግራም ከቤት የምትወጡ ካላችሁ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።

መንገዶች የሚዘጉት  80ኛውን የመቻል ስፖርት ቡድን ምስረታን ምክንያት በማድረግ በሚካሄድ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው።

ሩጫው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።

በዚህም ፦

- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ

- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ

- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት

- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ አንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት  #አዲስአበባ

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።

ስለሆነም ነገ ለስራ፣ ለቤተሰብ ለጓደኛ ጥየቃ ለሌላም ጉዳዮች ፕሮግራም የያዛችሁ ፕሮግራማችሁን ከልሱ።

መንገድ የሚዘጋው " ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም " በሚል የጎዳና ላይ ሩጫ ስለሚካሄድ ነው።

ሩጫው መነሻውን መስቀል አደባባይ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ከዛም በባምቢስ፣ ዑራኤል አደባባይ ወደ ቀኝ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ መስቀል አደባባይ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡

በዚህም  ፦
- ከ22 ወደ ዘሪሁን ህንፃ
- ከዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ
- ከአትላስ መብራት ወደ ዑራኤል አደባባይ
- ከቦሌ ሩዋንዳ መታጠፊያ ወደ ወሎ ሠፈር
- ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት መንገዶች
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ
- ከኤግዚብሽን ወደ ፊላሚንጎ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከቴሌ ማቋረጫ (ክቡ) ባንክ ወደ ስታድየም
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከካዛንቺስ ሼል (ኢንተር ኮንትኔታል ሆቴል) ወደ ባምቢስ
- ከዑራኤል አደባባይ ላይ እና ታች ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:30 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ከዛሬ ምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ በተጠቀሱ መንገዶች ላይ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ተከልክሏል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

በኮሪደር ስራ ምክንያት ፦

➡️ ከፊጋ መስመር ወደ ቀኝ ታጥፎ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ

➡️ ከጃክሮስ መስመር በኩል መብራቱን ተሻግሮ ወደ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ

➡️ ከኢፌዴሪ የማዕድን ሚኒስቴር ጫፍ ታጥፎ ወደ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ

ከዛሬ ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት አንስቶ ሙሉ ቀን እና ምሽት ለማንኛውም ተሽከርካሪ ዝግ እንደሆኑ ተገልጿል።

ሌላው ፤ ከአያት ወደ መገናኛ እና ከመገናኛ ወደ አያት ቀጥታ ማለፍ እንጂ አደባባዩን መዞርም ሆነ ማቋረጥ የተከለከለ ነው ተብሏል።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙም መልዕክት ተላልፏል።

መረጃው ከአ/አ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #መታወቂያ “ በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን ” - CRRSA ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው አዲስ አበባ ከተማ ለመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት በቅርብ ጊዜ መሰጠት ይጀመራል ተብሎ ነበር። ነገር ግን እስካሁን አገልግሎቱ አልጀመረም። ነዋሪዎችም መቼ እንደሚጀምር ጠይቀዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቼ ነው አገልግሎቱ መስጠት የሚጀምረው ? ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት…
#አዲስአበባ #መታወቂያ

“ የትምህርት ቤት ምዝገባው ሲጠናቀቅ አገልሎቱን መስጠት እንጀምለራለን ” - CRRSA

ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው አዲስ አበባ ከተማ ለመጡ ተገልጋዮች የመታወቂያ አገልግሎት “በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ እንጀምራለን” መባሉን ከወራት በፊት ነግረናችሁ ነበር።

አሁንስ ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ አገልግሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደምትሰጡ ከዚህ ቀደም ገልጻችሁ ነበር፤ ለመሆኑ ጉዳዩ ከምን ደረሰ? ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲን ዛሬ ጠይቋል።

የኤጀንሲው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮናስ አለማየሁ በሰጡት ምላሽ፣ አገልግሎቱን ለመጀመር ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዳጠናቀቁ ገልጸዋል።

“ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቀን ነበር ” ያሉት አቶ ዮናስ፣ “ ከተማ ውስጥ የትኛውም የየትምህርት ምዝገባ በልደት ካርድ መነሻ መሆን እንዳለበት አሰራር ዘርግተናል ” ብለዋል።

“ በዚህ መሠረት አሁን ባለው ሁኔታ ቢሮዎቻችን ይህንን አገልግሎት እየሰጡ ስለሆነ አብሮ ማስኬድ የማይቻል በመሆኑ ከትምህርት ቤት ምዝገባ በኋላ እንጀምራለን ” ሲሉ አክለዋል።

ከትምህርት ምዝገባ በኋላ መቼ እንደሚጀመር ቲክቫህ የጠየቃቸው አቶ ዮናስ፣ ከነሃሴ አጋማሽ 2016 ዓ/ም በኋላ እንደሆነ አስረድተዋል።

“ለዚህ የሚሆኑ ምቹ ሁኔታዎች አሉ” ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ “ሁሉም ወረዳዎች (119ኙም) በአሁኑ ወቅት ዲጂታላይዝድ ሆነዋል። አዲስ አበባ የወረቀት መመታወቂያ ለአንዴና ለመጨረሻ ተሰናብታለች ሰኔ ወር ውስጥ” ነው ያሉት።

“ ምቹ ሁኔታዎች አሉ። የማጭበርበር አዝማሚያም ካለ እጅግ በጣም Rare ነው የሚሆነው። ከክልል ከተማ የሚመጡት ሰዎች አገግሎቱን ሲያገኙም ጥብቅ የሆን ቃለ መጠይቅ ይኖራል ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ በቃለ መጠይቁ ውስጥ የምናገኛቸው ጉድለቶች፣ ግድፈቶች ካሉ አገልግሎቱን ልንከለክልበት የምንችል ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ” ብለዋል።

አቶ ዮናስ አክለው፣ “ ምክንያቱም ከክልል የሚቀርቡ መረጃዎችና መልቀቂያዎች ሀሰተኝነታቸው እየጨመረ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ እየሆነ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ ከፍተኛ ፍልሰት አዝማሚያው ምዝገባውን አግኝቶ ማስረጃውን ማግኘትም ጭምር ብቻ እንደሆነ አንዳንዱን ገምግመናል” ብለዋል።

“ በዚህ መልክ ተደራጅቶ እየተጠባበቀ ያለው ነዋሪ 47,000 ነው። ከዛ ውስጥ 40% ከአማራ ክልል፣ ኦሮሚያ ክልል 35%፣ ቀሪ የኢትዮጵያ ክልሎች 25% ሆኖ ተተንትኗል ” ነው ያሉት።

አክለው፣ “ ከእነዚህ ውስጥ ሃሰተኛ የሚያስመስሉ መሸኛዎች ያስገቡ መኖራቸውን አረጋግጠናል ” ብለዋል።

“ ጤነኛ የሆነ መሸኛ ይዞ የሚመጣ ደግሞ ይኖራል ” ያሉት አቶ ዮናስ፣ ህጋዊ የሆኑትን ለማስተናገድ ዝግጅታቸውን እንዳተጠናቀቁ፣ የት/ቤት ምዝገባ እንደተጠናቀቀ አገልግሎቱን መስጠት እንደሚጀምሩ አስረድተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ

1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ።

ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን አንድ የቤተሰባችን አባል መልዕክት አጋርቶናል።

ሹፌሩ ከመኪና ውስጥ አልወረደም ነበር። ምናልባት ቢወርድ ሌላ የነሱ ተባባሪዎች መኪናውን ይዘው ለመጥፋት አስበውም ሊሆን ይችላል ብሏል።

እነዚህ 3 ሰዎች ሁለቱ ከኋላ አንዱ ከፊት የነበሩ ሲሆን በፍጥነት የመኪናውን በር ከፍተው እቃ ይዘው ሲሮጡ ነው የተመለከታቸው።

" ፈጣሪ ነው የሚጠብቀን ነገር ግን በተለይ ምሽት ላይ ስንሰራ የምንጭናቸውን ሰዎች ፦
- ማንነት፣
- ስልክ ቁጥር ፣
- የምንሄድበትን ቦታ ፣
- የሰዎቹን ሁኔታ ድርጊታቸውን፣
- ንግግራቸውን በደንብ እንከታተል። ውስጣችን ጥሩ ስሜት ካልተሰማውም ይቅርብን " ብሏል።

ህይወታቸውን ለማሻሻል፣ ቤተሰባቸውን ለመደገፍ ፣ ልጆቻቸውን ለማኖር ሲሉ ብርድ እና ፀሀይ እየተፈራረቀባቸው ቀን ፣ ምሽት ፣ ለሊት ሳይሉ የሚሰሩ ወገኖቻችንን ፈጣሪ ከክፉ ይጠብቃቸው።

ዘራፊዎችም ዛሬ ላይ ተይዘው ነገ የሚለቀቁ ከሆነ ከወንብድና ተግባራቸው ስለማይመለሱ እጅግ ጠንካራ ቅጣት ሊጣልባቸው ይገባል።

የሰረቁበትን ቀን እንዲረግሙ የሚያደርግ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይገባል።

ሰው ለልጆቹ ፣ ለቤተሰቦቹ ለራሱ ህይወት ሲል ከባድ ዋጋ እየከፈለና በሰላም ጥሩ ሰራተኛ ዜጋ ሆኖ ሀገሩን ህዝቡን እያገለገለ ካለ በበቂ ሁኔታ ከወንጀል ሊጠበቅ ይገባዋል።

2. በመኪና ተደራጅተ የሚዘርፉ ዛራፊዎች አሁንም በከተማው አሉ።

በቅርቡ ፥ መካኒሳ አካባቢ አንድ ግለሰብ በገዛ ሰፈሩ ያውም ጠዋት ላይ በ " ቪትዝ " ተሽከርካሪ የመጡ ወንበዴዎች አንገቱን በማነቅ ንብረቱን ዘርፈው መሬት ላይ ጥለውት ጠፍተዋል።

" አውቶብስ ተራ " አካባቢ በተመሳሳይ አንድ ወጣት በ ' ቪትዝ ' ተሽከርካሪ ላይ በመሆንና ውሃ በመድፋት " ና እንጥረግልህ " በማለት ለመዝረፍ ሙከራ አድርገዋል ፤ ምንም እንኳ ክፉ ሃሳባቸው ባይሳካም።

እነዚህ ባለመኪና ወንበዴዌች ምናልባት ብዙ ቦታ መሰል ተግባራትን እየፈጸሙ ይሆናል።

ከወራት በፊት ሩወንዳ አካባቢ ለሊት በ ' DX መኪና ' ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ወንበዴዎች አንድን ግለሰብ ሞባይል ስልክ በገጀራ አስፈራርተው መዝረፋቸውን ነግረናችሁ ነበር።

መኪና የምታከራዩ ወይም መኪና ለሰው የምትሰጡት ሰዎችም ጥንቃቄ አድርጉ ማነው ፣ ለምን አገልግሎት እየተጠቀመ ነው የሚለውን አጣሩ።

ፖሊስ ይህንን ጉዳይ ከምንጩ ለማድረቅ መስራት አለበት።

በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመንገድ ትራፊክ መብራት ላይ ስርቆት በጅጉ ቀንሷል። ይህ አበረታች ተግባር ጭራሽ መኪና ይዘው ለዝርፊያ በተሰማሩ አካላት ላይም መቀጠል አለበት።

ሰዎች ቀንም ይሁን ማታ ሳይሳቀቁ መንቀሳቀስ እንዲችሉ መደረግ አለበት። ህግ ቀን ቀን ብቻ የሚሰራ ማታ የማይሰራ እስኪመስል ድረስ ዘራፊዎች የሚያደርጉን እንቅስቃሴ መገታት መቻል አለበት።

3. የጸጥታ አካላትን የሚመስል ልብስ ለብሰው የሚዘርፉም አሉ።

አንድ የቤተሰባችን አባል በመንገዱ የገመጠውን አጋርቶናል።

ድርጊቱ የተፈጸመው በዚህ ወር  አለርት ሆስፒታል አካባቢ ነው።

መኪናውን እያሽከረከረ በሚሄድበት ወቅት የጸጥታ ኃይል ልብስ የሚመስል የለበሱ በግሩፕ የተሰባሰቡ ሰዎች (8-10) ድቅድቅ ያለ ጨለማ ውስጥ ሆነው ሊያስቆሙት ይሞክራሉ።

ነገር ግን እውነተኛ እና ትክክለኛ የጸጥታ አካላት ሰዎች እንዳልሆኑ ይጠረጥራል። ምክንያቱም ከዚህ ቦታ በፊት (ብዙም ሳይርቅ) ሌላ የደህንነት ፍተሻ ተፈትሾ ነበር።

እንዚህ ሰዎች ቁም ያሉት ቦታ ድቅድቅ ጨለማ እና የሚያስፈራ ስለነበር ወደፊት ትቷቸው ሲሄድ ሁለት የተጎዱ ሰዎች መሬት ላይ ተኝተው ተመልክቷል። ሌላ መኪና ስላልነበረና ለህይወቱም በመስጋቱ በፍጥነት ከቦታው ርቆ ሄዷል።

ምናልባት እነዚህ ሰዎች ለፍተሻ ብለው መኪናቸውን አስቁመዋቸው ዘርፈዋቸው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬውን ገልጿል።

የፖሊስ የደህንነት ፍተሻ በጣም አስፈላጊ ቢሆንም ከየትኛውም አካል ፍቃድ ሳያገኙ ለመሰል እንቅስቃሴ የሚሰማሩ ካሉ አጥንቶ እርምጃ መውሰድ ይገባል። የማያዳግም አስተማሪ ቅጣትም መቀጣት ይገባል።

ሌላው የየትኛውም የሀገሪቱ የጸጥታ ልብስ በሲቪል ሰዎች / አባል ባልሆኑ ሰዎች እየተለበሰ በማኛውም መንገድ ሚዲያ ላይም ጭምር መታየት የለበትም። ሁሉም ሰው ለፍቶ ነው የክብር ልብሱን የሚለብሰውና ማንም እየተነሳ የጸጥታ ልብስ እየለበሰ መታየት ሌላውም ይህን እንዲለማመድ መደረግ የለበትም ፤ ልብሱም መከበር አለበት።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#አዲስአበባ

@tikvahethiopia