TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ ይህ #ድብድብ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራሷን በምታስተዳድረው #ሶማሌላንድ ፓርላማ ውስጥ የተከሰተ ነው።

ምንድነው የተፈጠረው ?

ዛሬ የፓርላማ አባላቱ ሞሃመድ አቢብ በተባለ የፓርላማ አባል ያለመከሰስ መብት መነሳት ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ ነበራቸው።

ሞሀመድ አቢብ እጅግ የሚታወቁና አውዳል ላይ ብዙ ተከታይ ያላቸው ፖለቲከኛ ሲሆኑ ገዢዎችን በመኮነን ለውጥ እንዲመጣ የሚታገሉ ናቸው ይባልላቸዋል።

የሶማሌላንድ መንግሥት እኚህን ፖለቲከኛ ከዛሬ 3 ቀን በፊት ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ዱባይ ሲመለሱ ሀርጌሳ ኤርፖርት ላይ ጠብቆ አስሮ እስር ቤት አስገብቷቸዋል።

ያሰራቸው በሀገር ክህደት እና የሶማሌላንድ ሪፐብሊክን ከሚቃወሙ ቡድኖች ጋር አብረዋል በሚል ነው።

ይህ በደጋፊዎቻቸው ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።

መንግሥት ፓርላማውን አስቸኳይ ስብሰባ አስቀምጦ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ በጠቅላይ አቃቤ ሕግ የውሳኔ ሀሳብ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም ከተገኙት 57 አባላት ውስጥ 51 አባላት ተቃውመዋል።

ታዲያ በዚህ ጉዳይ ላይ ነው ፓርላማ ውስጥ ክርክር ሲደረግ በሁለት አባላት መካከል የለየለት ድብደብ እና የቡጢ መሰነዛዘር፣ እቃ መወራወር የደረሰ መነጋገሪ ክስተት የተከሰተው።

ተደባዳቢ የፓርላማ አባላቱ መጎዳታቸው ተነግሯል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia