TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሁን

በትግራይ ስለተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የሽግግር ፍትህ በማረጋገጥ ሂደት ዙርያ ያለመ የውይይት መድረክ በመቐለ እየተካሄደ ይገኛል።

ውይይቱ ፤ የፍትህ ሚኒስትሩን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያካተተ የፌደራል ልኡካን ቡድን እንዲሁም የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ እንደሚገኝ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
* Update በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች ጋር 5 ሰዓታት የፈጀ ውይይት መደረጉ ተሰምቷል። ዛሬ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም የተመራ ልዑክ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት በአቶ ሽመልስ አብዲሳ ከተመራ የኦሮሚያ ክልል የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ጉዳይ ከቀኑ 9:00 እስክ ምሽት 2:00 ሰዓት ድረስ…
#አሁን

" በሸገር ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ብዛት ያለው መስጂድ ፈርሷል " - ሼህ ሐጂ ኢብራሂም

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም የተመራ ልዑክ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የኦሮሚፓ ክልል የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ጉዳይ የደረሱበትን ሁኔታ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እየተሰጠ ነው።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ባደረጉት ንግግር ፤ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ብዛት ያለው መስጊድ መፈረሳቸውን ገልፀዋል።

በንግግራቸው ፤ ድርጊቱን በመቃወም ሁሉም ሙስሊም ላደረገው ተጋድሎ በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ስም አመስገነዋል እንዲሁም ለመላው ሙስሊም መፅናናትን እና ሰብረን ተመኝተዋል።

መግለጫው አሁንም ቀጥሏል።

Credit : Harun Media

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አሁን

የነባሩ ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤውን በወልቂጤ እያደረገ ነው።

ነባሩ ክልል ስያሜውን ወደ " ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " የሚለውጥ ሲሆን ፦
- ህገ መንግስት ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድን መርምሮ ማፅደቅ፣
- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅ ቀርቦ ውይይት በማድረግ ማፅደቅ
- ልዩ ልዩ ሹመቶችን መስጠት የምክር ቤቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች መሆናቸውን የደ/ሬ/ቴ/ድ ዘግቧል።

ከነባሩ ክልል / ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጋር ተያይዞ የተቋማት መቀመጫዎች ጉዳይ የሰሞኑን አነጋጋሪ ጉዳይ እንደነበር ይታወሳል።

በተለይም በከምባታ ጠምባሮ ዞን በኩሉ ድልድሉ ፍትሐዊ አይደለም በሚል ተቃውሞ ተነስቶ ነበር። ከምስርታው ጉባኤ በፊት በህዝቡ ዘንድ ለተነሱ ቅሬታዎች ምላሽ እንዲሰጥ ተጠይቆ ነበር።

የዞን ምክር ቤቱም ድልድል የሠራው የጋራ ኮሚቴ በፍትሐዊነት የቢሮዎች ምደባን አላደረገም በሚል የፍትሃዊነት ጥያቄ ያነሳ ሲሆን በክፍፍሉ ጉዳይ የፌዴራሉ አካል ጣልቃ እንዲገባ በመስማማት ይህንን የሚጠይቅ ደብዳቤ በፅሁፍ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስገብቷል።

በሌላ በኩል ፤ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል ለመደራጀት በተስማሙት መሠረት አዲሱ የ " ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " የምስረታ ጉባኤ በጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

ፎቶ ፦ ደ/ሬ/ቴ/ድ

@tikvahethiopia
#አሁን #ሲዳማ

የሲዳማ ክልል ም/ ቤት አስቸኳይ ጉባዔ በሀዋሳ እያካሄደ ነው።

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው እያካሄደ ያለው።

ለአንድ ቀን ብቻ ይካሄዳል በተባለው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ በሶሰት የተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።

- ለጉባኤው ሞሽን ቀርቦ ይጸድቃል።

- የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ።

- የምክር ቤቱ አባላት #የህግ_ከለላ ማንሳት ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoP ነገ ማክሰኞ ጥዋት ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል። ምክር ቤቱ ስብሰባውን የሚያካሂደው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል። @tikvahethiopia
#Update #አሁን

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው፡፡

ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትም ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

እስካሁን ባለው ከተወካዮች ም/ ቤት አባላት ምን ምን ጉዳዮች ተነሱ ?

- የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ፣

- የሀገራዊ ትርክት ጉዳይ ፣

- የዜጎች ደህንነት ጉዳይ፣

- በየቦታው ያሉና ህዝቡን ሰላም እየነሱ ያሉ ታጣቂዎችን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንዳለ፤

- የትምህርት ጥራት አፈፃፀም፣ የመፅሀፍት እና የቁሳቁስ እጥረት ጉዳይ፣ በተጨማሪ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች እጣፈንታ ምንድነው ?

- ከባህር በር ጉዳይ ጋር ተያይዞ እንዲሁም በአጠቃላይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ስላለው የዲፕሎማሲ ሁኔታ፤

- ሰፊ የሀብት ብክነት እና ሌብነት የሚታይባቸው እንደ መሬት አስተዳደር፣ ገቢዎች  ፣ የጉምሩክ አገልግሎት ፣ ትላልቅ ግዢዎችና ትላልቅ የኮንስትራክሽን ስራዎች ከሌብነት እና ብክነት ለማፅዳት መንግስት ስለያዘው አቋም ፤

የሚመለከቱ ጥያቄዎች እና ሀሳቦች ተነስተዋል።

የሚሰጡት ምላሾችን እና ሌሎች ሀሳቦችን ተከታትለን እናቀርባለን።

@tikvahethiopia
#አሁን

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።

በስበስባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡት ስራዎች አሉት ፤ ስራዎቹን ፍፅሞ ስልጣኑ ያስረክባል " - አቶ ጌታቸው ረዳ ትናት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ ከነሀሴ 9 አስከ 11/2016 ዓ.ም  " ትግራይ ከአስከፊውና ደም አፋሳሽ  ጦርነት ወደ ከፍታ ወይስ ወደ ብዥታ ጉዞ !! " በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የትግራይ ሙሁራን ማህበር ያዘጋጀው የውይይት መድረክ…
#አሁን : በመቐለ ከተማ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ በወቅታዊ የህወሓት የፓለቲካ ሁኔት ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ መድረኩ ላይ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " ብለው የተቃወሙ ፦
➡️ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ፣
➡️ የድርጅቱ የማእከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን ፣
➡️ የክልል ፣ የዞን ፣ የወረዳና ሌሎች አመራሮች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ፥ " የውይይት መድረኩ ህወሓትን ለማዳንና ትግራይን ወደ ነባራዊ ሁኔታዋ ለመመለስ ወሳኝ ነው " ማለታቸውን ከድምጺ ወያነ ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ተጨማሪ ይኖረናል።

የፎቶ ባለቤት ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia