TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

ሰሞኑን " ዶላር በጣም ጨምሯል " በሚል የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ የሚገኙ የንግዱ አካላት እጅግ እያማረሯቸዉ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤት ብለዋል።

" አሁን ላይ ነጋዴው እቃውን በሌሎች ነጋዴዎች ሱቅና በራሱ መጋዘን ሲያስቀምጥ አይናችን እያዬ እቃዉ የለም በሚል ዋጋ ሊጨምር ሲሞክር ማየት ያማል " ሲሉ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ፥ " እስከ 1,080 ብር የነበረዉ ዘይት 1380 ብር ሲገባ ዶላር ነው " አሉን " እሺ የቲማቲምና ሽንኩርቱስ ዋጋ መናር ከየት መጣ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

1 ኪሎ ሽንኩርት ከ40 ብር ተነስቶ 90 ብር ቲማቲም 20 ብር የነበረው 40 እና 45 መግባቱን ጤፍም በኪሎ ከ10 ብር በላይ እንደጨመረ ጠቁመዋል።

ስሚንቶ ላለፉት ወራት ጥሩ ቢሆንም አሁን ላይ " የለም " እየተባለ እንደሆነ ገልጸዋል።

የነዳጅ ጉዳይ ግን በፊትም አንስቶ ፈተና ነበር አሁን ብሶበት ራስ ምታት ሆኖ ቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

ሀዋሳ ላይ የገበያውን ሁኔታ ስርአት ለማስያዝ የተቋቋመ ግብረሀይል መኖሩን በመስማታችን  የነዋሪዎችን ቅሬታ ይዘን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዡ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለን አነጋግረናል።

እሳቸውም ፥  " አሁን ላይ እቃ በሚደብቁ እና አላግባብ ዋጋ በሚጨምሩ ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ ግብረሀይሉ  ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው " ብለዋል

ግብረሀይሉ  በሰራዉ ስራ ሁለት ማደያዎች እና 62 የሸቀጣሸቀጥ ሱቆች የምግብ ግብአትና የብረታብረት አቅራቢዎች በ8ቱ ክፍለ ከተሞች  መታሸጋቸዉንና እቃዎችም ተወርሰዉ ህገወጦቹ ግለሰቦች  በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ገልጸዋል።

ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚገልጹት አዛዡ ማህበረሰቡም ህገወጦችን በመጠቆም የፖሊስን ስራ እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#የአሽከርካሪዎችድምፅ

“ በአምስት ቀናት ውስጥ 7፣ ባለፉት ዓመታት ከ170 በላይ ሾፌሮች በሽፍቶች ተገድለዋል፡፡ ወደ 90 የፎቶ ማስረጃዎች አሉን ” - ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር

አሽከርካሪዎች በተለያዩ ቦታዎች ላይ በ " ሽፍቶች " መታገት እና መገደላቸው እንዳልቆመ፣ መንግስትም ሆነ የመንግስት ሚዲያዎች ለችግሩ ትኩረት እየሰጡ እንዳልሆነ ሾፌሮችና ጣና የከባድ መኪና አሽርካሪዎች ማኀበር ምሬታቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቤት ብለዋል፡፡

ለቲክቫህ ኢትዮጵካ ቃሉን የሰጠው ማኀበሩ ፣ ሰሞኑን እንኳ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን 5 ሹፌርና ረዳት፣ አንድ ነጋዴ እንደተገደሉ፣ ሁለት ሰዎች ታፍነው እንደተወሰዱ ገልጿል፡፡

" መንገዱ የሱዳን ቦርደር (ድንበር) ነው፡፡ ሽንኩርት ኢምፖርት የሚደረግበት፣ ቡና፣ ባቄላ ኤክስፖርት፣ የሚደረግበት ዋና መንገድም ነው፡፡ ነገር ግን ሽፍታ ነው የሚፈነጭበት፡፡ በተደጋጋሚ ነው ይሄ ችግር የተከሰተው፡፡ ሰሚ አካላ የለም፡፡ በቃ አሽከርካሪውም ከመሄድ መቆጠብ አለበት " ብሏል፡፡

" በአምስት ቀናት ውስጥ ብቻ 7፣ ባለፉት ዓመታት ከ170 በላይ ሾፌሮች በሽፍቶች ተገድለዋል፡፡ ወደ 90 የፎቶ ማስረጃዎች አሉን፡፡ ከዛ ውጭ በማኀበራዊ ሚዲያ ያልወጣ፤ በየቦታው እተዳፈነ የቀረ ነፍስ አለ " ነው ያለው፡፡

" ችግሩ በየአካባቢው አለ " የሚለው ማኀበሩ ፣ " በኦሮሚያ ክልልም ከመተሐራና ወለጪቲ መካከል ከፍተኛ የስጋት ቀጠና ነው፡፡ ሾፌር ይዘረፋል፤ ይገደላል፤ ማንም ሳላልተቆጣጠረው ጥቃቱ አልቆመም " ሲል ወቅሷል፡፡

" በቅርቡ ደባርቅ ላይ የተገደለ ሾፌር አለ፡፡ ሁመራ መስመር ላይም የተገደለ ሹፌር አለ፡፡ በሁመራው መስመር የተገደለው ያውም የመከላከያዎችን ግዳጅ ጭኖ እየሄደ ነው፡፡ በአንድ ቀን 5 ሾፌርና ረዳት የሚገደልበት አሰቃቂ ሁኔታ ነው ያለው " ብሏል፡፡

" ትልቁ ክፍተት ፀጥታ የማስከበር ሂደቱ መላላት ነው፡፡ አግቶ ስልክ ተደደዋውሎ ገንዘብ የሚቀበልን ሽፍታን ስልክ በጂፒኤስ ጠልፎ ተከታትሎ እርምጃ መውሰድ ይቻላል፡፡ የተወሰነ ቦታ ላይ እንዲህ ቢደረግ ማንም ይህን ድርጊት አይሞክረውም " ሲል አስገንዝቧል፡፡

" ' ቴክኖሎጂውን ታጥቀናል ' እየተባለ ቴክኖሎጂው የዜጎችን ሕይወት ካልታደገ ምን ያደርጋል ? " ሲል ጠይቋል፡፡

አሽከርካሪዎችስ ምን አሉ ?

" መንግስት ሁሌ ህግ ያስከብር፤ ጥበቃ ያድርግልን ብለን ለፍልፈናል፡፡ በቃ ጉዳያችሁ አይመለከተኝም ብሎናል ማለት ነው፡፡

አሽከርካሪዎች ያላቸው አማራጭ ራሳቸውን በራሳቸው ማስከበር ነው፡፡

ችግር ወዳለበት ቦታ ባንሄድ እኮ ግብዓት ማቅረብ ሲቆም መንግስት መንገዱን ይጠብቀው ነበር፡፡

ስለዚህ አሁን የምንወቅሰው ራሳችንን ነው፡፡ ሾፌር የጫነውን ጤፍ የሚመገብ ሽፍታ ነው ሾፌርን የሚገድለው፡፡ ስለዚህ ሾፌሩም ጤፍ መጫን አቆሞ ያንበረክከዋል፡፡

ህዝብን የሚያገለግል ሾፌር ነው የሚገደለው፡፡ ስለዚህ ህዝብም አገልግሎት ሲቋረጥበት መንገዱን ወጥቶ ይጠብቃል፡፡ በቃ! መፍትሄው ይሄው ብቻ ነው፡፡

ለአመታት በተደጋጋሚ ሹፌር እየተገደለ፣ እየታገተ ስለጉዳዩ የሚዘግብ የመንግስት ሚዲያ የለም፡፡ ጎንደር ላይ ሰሞኑን እንኳ ለአገር ትልቅ አበርክቶ ያላቸው 6 ነፍሶች ወድቀው ቀርተዋል፡፡ ግን ማንም ጉዳይ አላለውም
" ሲሉ በምሬት ተናግረዋል፡፡

ስለጉዳዩ ከዚህ ቀደም የጠየቅነው የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ሚኒስቴር ችግሩ እየቀነሰ እንደሆነ ነበር የገለጸው፣ አሽከርካሪዎች ግን እንዳውም ችግሩ እየባሰ ሂዷል ባይ ናቸው፡፡

የሚመለከታው አካላት ለጉዳዩ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፣ ከሆኑ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጥ የሆነ የአካዳሚክ ካላንደር መተግባር እንደሚጀምር ተሰምቷል።

በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተፃፈ ደብዳቤ ተመልክተናል።

ደብዳቤው ከትምህርት ሚኒስቴር የወጣ እና ትክክለኛ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደብዳቤው ከደረሳቸው የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች አረጋግጧል።

ደብዳቤው ከ2017 ትምህርት ዘመን ጀምሮ ወጥ የሆነ የአካዳሚክ ካላንደር በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መተግባር እንደሚጀምር ይገልፃል።

በዚህም፦

- የ1ኛ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ፦ መስከረም 7 እና 8/2017 ዓ.ም

- የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሁሉም መርሐግብር ተማሪዎች ምዝገባ፦ መስከረም 9 እና 10/2017 ዓ.ም

- የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሁሉም መርሐግብር የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት መስከረም 13/2017 ዓ.ም ይጀመራል።

የ2017 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 27 ድረስ ይሰጣል።

(ሙሉው የ2017 ትምህርት ዘመን የአካዳሚክ ካላንደር ከላይ ተያይዟል።)

ምንጭ ➡️ @tikvahuniversity
#Tigray

" ሁሉም ትግራዋይ ወዴት እያመራን ነው ? ብሎ ራሱን በራሱ በመጠየቅና በመመለስ የመፍትሄ ሃሳብ መስጠት ይገባዋል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በመቐለ ከተማ ዓለም አቀፍ የትግራይ ሙሁራን ማህበር (GSTS) ለ3 ቀናት ያዘጋጀው ትግራይ ክልል መልሶ በማቋቋም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ጀምሯል።

በመክፈቻው መርሃ ግብር ፦

➡️ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ

➡️ ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በም/ ፕሬዝዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደርና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ

➡️ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር።

በመክፈቻው አቶ ጌታቸው ንግግር አድርገዋል።

በዚህም ፥ " ሁሉም ትግራዋይ ወዴት እያመራን ነው ? ብሎ ራሱን በራሱ በመጠየቅና በመመለስ የመፍትሄ ሃሳብ መስጠት ይገባዋል " ብለዋል።

" ያለውን መድረክ በመገንዘብ የመፍትሄ ሃሳብ በማስቀመጥ የበኩሉ ሃላፊነት መወጣት አለበት " ሲሉም ተናግረዋል።

" የሙሁራኑ ውይይት ማንኛውም ፓለቲካዊ ልዩነት ይኑር ችላ መባል እና መታለፍ የሌለባቸውን በመያዝ እንዲጠሩ መስራት ይጠበቅበታል " ሲሉ አስገዝበዋል።

ለ3 ቀናት ይቆያል በተባለው የውይይት መድረክ በርካታ ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርባሉ ፣ ውይይትም ይደረጋል ተብሏል።

ከመላው ኢትዮጵያ ጨምሮ ፥ ከአፍሪካ ፣ አሜሪካ ፣ አወሮፓና ልሎች የዓለም ክፍሎች የተጋበዙ የትግራይ ሙሁራን ተሳታፊ እንደሆኑ ተሰምቷል።

ፎቶ ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia 
#DireDawa

" አንዳንዴ አላህን መፍራት ያስፈልጋል። ክርስቲያም ከሆን የምናመልከውን ፈጣሪን መፍራት ያስፈልጋል።

ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል።

በአንድ ለሊት የውጭ ምንዛሬው ሲጨምር ባንክም ውድድር ውስጥ ገብቷል።

ግን እዚሁ ስቶር የነበረውና ከ3 ወር በፊትና ከዛ በፊት የገቡ እቃዎች በአንዴ 300 ፐርሰንት መጨመር ሃጢያት አይደል ? አላህ እራሱ ይወደዋል ወይ ?

የሃላል ነገር ነው አይደል ሰው መብላት ያለበት፤ ይሄ ድሃ ማህበረሰብ ነው ሁሌ እናተን በችግር ጊዜ የሚያግዛችሁ።

ቢያንስ ለ3 ወር ! በአዲሱ ምንዛሬ ሲገባ ያኔ እኮ ባላንስ ይደረጋል ፤ ምን ነበር የሚለውን ማየት ይቻላል።

ወደ እርምጃ ሲገባ ግን የከፋ ይሆናል።

እውነቱን ለመነጋገር ከእናተ የድሃውን ማህበረሰብ እምባውን ማበስ ይሽለናል። በግልጽ ለመነጋገር።

ለሰው ብላችሁ አይደለም፤ ለማንም ብላቹ አይደለም ለህሊናችሁ ብላችሁ ስሩ፤ ዛሬ የዘራችሁትን ነገ ልጆቻችሁ የተሻለ ነገር ያገኛሉ። "

የድሬዳዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር (በቅርቡ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በነበራቸው ውይይት የተናግሩት)

#DireDawaCity

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ፣ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ከኢትዮጵያ መንግሥት የተበረከተላቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " አልቀበልም " ብለው መልሰው ከመድረክ መውረዳቸው ይታወሳል። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር " ገንዘቡ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ ይሆናል። ምክንያቱም ስጦታ በግድ ውሰዱ ስለማይባል " ሲል ለኤፍ ኤም 97.1 ተናግሯል። አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ፤ ለሙያውና…
#GemedoDedefo

ከፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ እጅ የተሰጣቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " የኛ የአሰልጣኞችን ልፋት አመጥንም " ብለው ሳይቀበሉ የቀሩትና በኃላም " እዛ ቦታ ላይ ያን ማድረግ አልነበረብኝ ፤ ተሳስቻለሁ " በማለት ህዝቡን እና ፕሬዜዳንቷን በይፋ ይቅርታ የጠየቁት አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ዛሬ " ታስረዋል " ከሰዓታት በኃላ ደግሞ  " ከእስር ተፈተው ወደ ቤት ገብተዋል " የሚሉ መረጃዎች ሲሰራጩባቸው ነበር።

እሳቸው ግን " እኔ አልታሰርኩም ፤ እስር ቤትም አልነበርኩም  " ሲሉ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ዙሪያ ታማኝ ነው የሚባለው ጋዜጠኛ ኤቢሳ ነገሰ አሰልጣኙን በስልክ እንዳገኛቸውና " ጉዳዩም እንደሚባለው እንዳልሆነ "  ገልጿል።

እሳቸው አሰልጣኝ ገመዶም እስር ቤት እንዳልነበሩ ቃላቸውን እንደሰጡት አመልክቷል።

" እኔ አልታሰርኩም " ማለታቸውን ጋዜጠኛው አሳውቋል።

በሌላ በኩል አሰልጣኙ በራሳቸው የፌስቡክ ገጽ መታሰራቸው " ውሸት ሀሰተኛ ዜና " እንደሆነ እና ቤታቸው እንደሚገኙ ገልጸው ወዲያው ደግሞ አጥፍተውታል።

ጉዳዩን ከሚያውቁ ሌሎች አካላት በተገኘው መረጃ ግን አሰልጣኙ ታስረው እንደነበር ፤ ምሽት ላይ ግን መፈታታቸው ተሰምቷል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አሰልጣኙ " አልወስድም " ያሉት  ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ እንደሚሆን ማሰወቁ ይታወሳል። " ስጦታ በግድ ውሰዱ አይባልም " ነው ያለው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia አትሌቲክሳችን ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገዋል። ይህ መሆን ያለበት ደግሞ በትክክለኛ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ነው። የኦሎምፒክ ውጤቱ አንገት የሚያስደፋ ነው። በጭቅጭቅ፣ በንትርክ፣ በየሚዲያ ላይ በሚደረግ ምልልስ የተጀመረው የፓሪስ ውድድር ኢትዮጵያን የማይመጥን እጅግ ዝቅ ያለ ውጤት ተመዝግቦበት አልቋል። ጥፋት ከደረሰ እና ውጤት ከጠፋ በኃላ የሚቀርብ ይቅርታ ተቀባይነት የለውም። …
#Ethiopia

" ኢትዮጵያ ፓሪስ ላይ በአትሌቲክሱ ያስመዘገበችው ዝቅተኛ ውጤት በቀናት ውስጥ ተረስቶ አጀንዳው ተቀይሯል።

ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት ኃላፊነቱን የሚወስደው ማነው ? ቀጣዩ እርምጃስ ምንድነው ? ወይስ ጉዳዩ ተረሳስቶ ይቀራል ነው ?

ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ስሟ ከፍ ብሎ የሚጠራባት አትሌቲክስ ታሟል። ስለሆነም ስር ነቀል ለውጥ መምጣት አለበት።

ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው የአትሌቲክስ ሰዎች ሁሉ ቁጭ ብለው መክረው ለውጥ ያምጡ።  

ዳግም ህዝብ በሚኮራበት #አትሌቲክስ እንዳያዝን እና እንዳይበሳጭ ዘላቂ መፍትሄ በአስቸኳይ መፈለግ አለበት።

ለነገ ዛሬ ካልተሰራ ተመሳሳይ ነገር ይጠብቀናል። " @nousethiopia

@tikvahethiopia
#Oromia

" አገልጋይ ካህንን ጨምሮ 6 ምዕመናን በታጣቂዎች ተገድለዋል " - ነዋሪዎች

በአርሲ ሀገረ ስብከት፣ በአሰኮ ወረዳ በጢዮ ቀበሌ ጠለታ ጨፋ ከተማ " የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን " አገልጋይ ካህንን ጨምሮ 6 ምዕመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎቹን ዋቢ በማድረግ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ካህኑ ሥጋ ወደሙን አቀብለው ምእመናንን እያሳለሙ በነበረበት ሰዓት ነው የተገደሉት።

3 ምዕመናን ከባድ ጥቃት ደርሶባቸው በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ነዋሪዎቹ ድርጊቱን የፈጸሙት " ኦነግ ሸኔ " ተብለው የሚጠሩ ታጣቂዎች ናቸው ብለዋል።

ግድያው የተፈጸመው ከነሐሴ 7 ቀን 2016 ዓ / ም ጀምሮ እንደሆነ ነዋሪዎቹ አመልክተዋል።

ከዚህ ባለፈም ፥ በተለያየ መንገድ ቤተ ክርስቲያኗን ሲረዱ የነበሩ ምዕመናን ተለይተው ሀብት እና ንብረታቸው መቃጠሉንና የአካባቢው ምእመናን ቤታቸውን ትተው በዱር በስጋት ውስጥ እንደሆኑ ተጠቁሟል።

ጥቃቱ ከዚህ ቀደምም ተፈጥሮ እንደነበር አንስተው " ለበላይ አካል ብናሳውቅም ጩኸታችንን የሚሰማ አጥተናል " በማለት ጥሪ ማቅረባቸውን ከቴሌቪዥን ጣቢያው የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ ° “ ጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን በደብዳቤ ሽሮ ከእጥፍ በላይ ቀረጥ ‘ ክፈሉ ’ እያለን ነው ” - አስመጪዎች ° “ ከአፈጻጸም አኳያ ምን ሊያስቸግረን ይችላል ? የሚለውን ውይይት እየተደረገ ነው ” - ጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ ኮሚሽን ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ምክንያት በማድረግ ከተቀመጠው አዋጅ ውጪ የቀረጥ ክፍያ እየጠየቃቸው መሆኑን አስመጪ ነጋዴዎች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቤት ብለዋል፡፡…
#ጉምሩክ

➡️ “ ከፍተኛ የወደብ ኪራይ የኮንቴነር ዲመሬጅ በየቀኑ እየጨመረብን ነው ” - አስመጪዎች

➡️ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” - ጉምሩክ ኮሚሽን

አስመጪዎች ፣ ተግባራዊ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን የሚተካ ' አዲስ መመሪያ ' በማውረድ እስከዛሬ ሲከፍሉት ከነበረው ቀረጥ ከእጥፍ በላይ ካልከፈሉ እቃቸውን መውሰድ እንዳይችሉ እያደረጋቸው መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው የጉምሩክ ኮሚሽን፣ “ አስመጪዎቹ የሚያነሳቸውን ጉዳዮችን ኮሚሽኑ ተረድቷል፡፡ ከህግ አንጻርም ምን መሆን ነው ያለበት ? ከአፈጻጸም አኳያስ ምን ሊያስቸግረን ይችላል ? የሚለውን ውይይት እየተደረገ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር፡፡

አስመጪዎቹ ዛሬስ ምን አሉ ?

“ ምንም የተቀየረ ነገር የለም፡፡ አሁንም ከዶላር ጭማሬው በፊት ለተመዘገቡት እቃዎች መፍትሄ አልተሰጠም፡፡ ወቅታዊ ስራ እያለፈን ነው፡፡ ከፍተኛ የወደብ ኪራይ የኮንቴነር ዲመሬጅ በየቀኑ እየጨመረብን ነው፡፡

በሌላ በኩል ፥ ለተማሪዎች መገልገያ የሚሆኑ ዕቃዎች አሉን፡፡ ይህ ጊዜ አለፈን ማለት እቃው ለአንድ ዓመት መጋዘን ነው የሚቀመጠው፡፡ ብዙ ጊዜ የሚያልፍባቸው ዕቃዎችም ይኖራሉ ምግብ እና መድኃኒቶች ” ብለዋል፡፡

ኮሚሽኑ ትላንትና (ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) የተወሰነ ማሻሻያ አድርጎ ከሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ/ም ወዲህ ለተመዘገቡት እቃዎች መልቀቂያ እንዲሰጥ በቃል ትዕዛዝ ሰጥቶ እንደነበር ፤ ነገር ግን ‘ ከጉምሩክ ፕሮሰስ ደብዳቤ ነጻ ነህ ’ ተብሎ መልቀቂያ የሚሰጥበት ክፍል ‘ ደብዳቤ አልደረሰኝም ’ እያለ መሆኑን ገልጸዋል።

ኮሚሽኑ ውይይት ማድረጉን መግለጹ መልካም ሆኖ እያለ፣ ለውሳኔ በዘገዬ ቁጥር ብዙ አሉታዊ ተፅዕኖዎች እንደሚደርሱባቸው ገልጸው፣ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ በሰጡን ምላሽ፣ “ ኮሚሽኑ እየሰራበት ነው በጉዳዩ ላይ፡፡ ምናልባት ነገ ምላሽ ይሰጣል፡፡ ሌላው ጉዳይ ካልዘገዬ በስተቀር ነገ (ነሐሴ 10) ምላሽ ይሰጣል ብዬ ኤክስፔክት አደርጋለሁ ” ብለዋል፡፡

“ ነገ ጠብቁ ፣ ብቻ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ብዬ ነው ኤክስፔክት የማደርገው ” ነው ያሉት።

(አስመጪዎቹን ቅር ያሰኘው የኮሚሽኑ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

ስልክዎን በአቢሲንያ POS ማሽኖች ላይ በማስጠጋት በዲጂታል ካርድዎ ቀለል አድርገው ይክፈሉ።

መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

#DigitalVisacard #Visa #ApolloVisacard #BoAVisacard #Visacard #Digitalethiopia #Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
#Infinix_Note40_Pro_Plus

አዲሱ የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ከፍተኛ ጥራት ያለው 108 ሜጋ ፒክስል ካሜራው በተለያዩ አማራጮች ቁልጭ ያለ ፎቶን ይሰጦታል በተጨማሪም የሱፐር ዙም ቴክኖሎጂው ከርቀት ሆነው ጥራት ያለው ምስልን ማንሳት ያስችላል፡፡

#Note40Et #Note40Pro #Note40 #Note40ProPlus #InfinixEt
🔈#የመምህራንድምጽ

° " ግንባታው እንዲቆም ተደርጎብናል " - መምህራን

° " ጉዳዩን የጸረሙስና አካላት ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል፤ ምርመራ ተጀምሯል " - የሀዋሳ ፖሊስ

ከሰሞኑን " በማህበር ተደራጅተን የምንገነባውን የመኖሪያ ቤት ግንባታ በማስቆም እንዲገነባልን ውል የገባውን ተቋራጭ አሰሩብን " ያሉ የሀዋሳ ከተማ መምህራን ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

መምህራኑ " አመራሩ ሊደግፈን ሲገባ እየገፋን ነው " ብለዋል።

" በሀገሪቱ ጠ/ ሚኒስትር ሳይቀር ለመምህራን ድጋፍ ተደርጎ የቤት ባለቤት የምንሆንበት መንገድ ይመቻች በተባለበት በዚህ ወቅት መምህራን የሚገነቡትን ቤት አስቁሞ ተቋራጭን ማሰር መንግስትና መምህራንን ለማጋጨት የታሰበ ሴራ እንጅ ሌላ ምንም አይደለም " ብለዋል።

" ድርጊቱ አሳፋሪ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

መምህራኑ፤ ከሳምንት በፊት አመራሩ በመምጣት " በርቱ " እንዳላቸውና ከፌደራል ሳይቀር እንግዳ ጋብዞ ፣ እገዛ ልናደርግ ዝግጁ ነን " እንዳላቸው ተናግረዋል።

በድንገት ግን ተገልብጦ ስራው ህጋዊ አይደለም ማለቱን ጠቁመዋል።

" ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በውይይት ማስተካከል ይቻላል " የሚሉት መምህራኑ ለ9 አመታት የቆመ ቤት ድንገት መሰራት ሲጀምር ለማስቆም መሯሯጥ ከጀርባው ሌላ ዓላማ ያነገበ እንዳይሆን ስጋታቸውን ገልጸዋል።

መምህራኑ ህጋዊ በሆነ መንገድ የሚያሰሩትን የህንጻ ዲዛይን ከG+3 ወደ G+4 መቀየራቸውን የከተማው ማዘጋጃ ቤት የማህበራት ማደራጃ እና የከንቲባ ጽህፈት ቤት የሚያውቀው እንደሆነ ጠቁመዋል።

ይህ ሆኖ እያለ ግንባታው #እንዲቆም መታዘዙን ገልጸው ፤ " ወቅቱ መምህራን የሚደገፉበት እንጅ ጥሪታቸውን ያፈሰሱበትን የሚቀሙበት አይደለምና እንቅፋት የሆኑብን አካላት ሊተዉን ይገባል " ብለዋል።

" በህግ አምላክ እጃችሁን ከድሀው መምህራን ላይ አንሱልን ፤ ይህ ባይሆን ግን አደባባይ በመውጣት ጩኸታችንን ለማሰማት ዝግጁ ነን " ሲሉም ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የከተማው አስተዳደር ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ በአጠቃላይ ለስድስት የመምህራን መ/ቤቶች ህብረት ስራ ማህበራት የጻፈውን ደብዳቤ ደርሶት ተመልክቷል።

በዚህም ደብዳቤው ፦

- የነበረው ዲዛይን ከG+3 ወደ G+4 ማስተካከያ እንዲደረግ ተጠይቆ የG+4 ዲዛይን መሰጠቱ ፤

- ነገር ግን ይህ ዲዛይን የመምህራን መ/ቤቶች ማህበራት ከተደራጁበት አላማ አንጻር ተጻራሪ ዓላማ እንዳለው ስለተደረሰበት የG+4 ዲዛይን መሰረዙን ሌላ ደብዳቤ እስኪላክላቸው ድረስ ቀድሞ በነበረውም G+3 ዲዛይን ግንባታ ማካሄድ እንደማይችሉ ያዛል።

የመምህራኑን ጥያቄ ይዘን ጥያቄ ያቀረብንለት የከተማው ፖሊስ ጉዳዩን የጸረሙስና አካላት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዉ ምርመራ እንደጀመሩበት በመግለጽ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጉምሩክ

(አስመጪዎች)

" በኢንቮይስ ያልተከፈሉ አሉ። ብዙ እቃዎች ናቸው ያሉት። እቃዎቹ አንድ ላይ ጉምሩክ የገቡ ናቸው።

የነዛና የነዚህ ልዩነት በጣም ሰፊ ነው። ከ4 እስከ 5 ሚሊዮን በኮንቴነር ጭማሪ የሚያመጡ ናቸው።

እነዚህም አብረው የሚስተናገዱበት መንገድ መኖር አለበት።

እቃዎቹ ሰሞኑን የታሪፍ ፣ የቀረጥ ለውጥ ሁሉ ተደርጎባቸው ነበር። በአንድ አይተም እስከ 10 ዶላር ጭምር ተደርጎ ነበር ከሬት ውጭ እሱ ላይ ብዙ ቅሬታ አልነበረም ሁሉም አንድ ላይ ስለጨመረበት።

አሁን ላይ እቃው አብሮ ገብቷል። እነዚህ ኢንቮይስ ከፍለዋል። እኛ በኢንቮይስ አልከፈልንም። ተመሳሳይ እቃዎች ናቸው።

የእነሱ ይውጣ ፤ እናተ ደግሞ በአዲሱ ሬት ክፈሉ ብንባል በጣም ትልቅ ልዩነት ይኖራል። በአንድ ገበያ ላይ ተወዳድሮ ለመስራት የሚቻል አይደለም።

ጉምሩክ ይኔንም ስጋታችንን ቢይይልን።

ሁለት ቦታ ተከፍለናል ፤ በኢንቮይስ የከፈሉ አሉ በኢንቮይስ ያልከፈልን አለን። ልዩነቱ ብዙ ነው በሚሊዮኖች ነው።

አንድ ገበያ ላይ  ነው የምንሰራውና እኛንም ከገበያ እንዳያስወጣን ይሄም ይታይልን። "

#CustomsCommission

@tikvahethiopia