TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ስፖርት

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን U23 በማሊ አቻው 4 ለ 0 በሆነ ውጤት #ተሸንፏል#MALI 4 - 0 #ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ስፖርት ፦ ዛሬ ምሽት በመላው ዓለም የእግር ኳስ ወዳጆች ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ይካሄዳል።

የዚህ የዋንጫ ፍልሚያ የሚካሄደው በሊቨርፑል እና ሪያልማድሪድ መካከል ሲሆን በመላው ዓለም ሚሊዮኖች ይህንን ጨዋታ ይከታተሉታል።

የስፖርት ወዳጅ የሆናችሁ የቤተሰባችን አባላት ጨዋታውን የተመለከቱ መልዕክቶች እንዲሁም ጎሎች በቲክቫህ ስፖርት በኩል ይደርሳችኃል https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport
#Ethiopia 🇪🇹

ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትካፈልበት ተጠባቂው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ ለሊት ይጀምራል።

ዛሬ ለሊት አትሌቶቻችን ውድድራቸውን ያካሂዳሉ።

በዚህም መሰረት :-

- ሌሊት 9:15 :- የወንዶች 3,000 ሜትር መሰናክል ማጣርያ

🇪🇹 ለሜቻ ግርማ
🇪🇹 ጌትነት ዋሌ
🇪🇹 ኃይለማሪያም አማረ

- ሌሊት 10:10 :- የሴቶች 1,500 ሜትር ማጣርያ

🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ
🇪🇹 ፍሬወይኒ ኃይሉ
🇪🇹 ሒሩት መሸሻ

የ " ኦሪጎን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር " በDSTV ልዩ ቻናል እና ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ መዝናኛ ቻናሎች በቀጥታ መከታተል ይችላሉ ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ #ስፖርት https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport
#ስፖርት

በመላው ዓለም እጅግ ከፍተኛ ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የእግር ኳስ ፍልሚያ የ " 2022/23 የውድድር ዓመት " ሻምፒዮን #ማንችስተር_ሲቲ መሆኑ ዛሬ ቅዳሜ ተረጋገጠ።

ማንችስተር ሲቲዎች ምንም እንኳን በውድድር ዓመቱ ቀሪ ጨዋታዎች ቢኖራቸውም ብርቱ ተፎካካሪያቸው #አርሴናል ዛሬ በኖቲንግሃም ፎረስት መሸነፉን ተከትሎ የዋንጫው ባለቤት መሆናቸውን ከወዲሁ አረጋግጠዋል።

ማንችስተር ሲቲዎች ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት የሊጉ ሻምፒዮናነትን ሲያሸንፉ በክለቡ ታሪክ ዘጠነኛው ሆኗል።

ተጨማሪ ፦ https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport    
#ስፖርት

ማንችስተር ሲቲ የእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ 2023/2024 ሻምፒዩን ሆነ።

ቡድኑ በተከታታይ ለ4 ዓመታት የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ በማንሳት አዲስ ታሪክ ጽፏል።

ዘንድሮ እስከ ዛሬው የመጨረሻ መርሀግብር ከ #አርሴናል ጋር አንገት ለአንገት የተናነቀው ሲቲ 91 ነጥብ በመሰብሰብ ነው ዋንጫውን ያሸነፈው።

እጅግ ብርቱ እና ጠንካራ አመትን ያሳለፈው አርሴናል 89 ነጥብ በመያዝ በሁለተኛነት ማጠናቀቅ ችሏል።

አርሴናል ባለፈው አመትም ለዋንጫ ተቃርቦ ዋንጫውን ማግኘት ሳይችል መቅረቱ አይዘነጋም።

ዘንድሮም በ2 ነጥብ ተበልጦ ዋንጫውን ሳያገኝ ቀርቷል።

ሊቨርፑል አመቱን በ3ኛነት ሲያጠናቅቅ አስቶን ቪላ 4 ፣ ቶተንሃም 5 እንዲሁም ቼልሲ 6 ሆነው ጨርሰዋል።

ባለ ብዙ ታሪኩ ማንቸስተር ዩናይትድ እጅግ በጣም ደካማ የተባለ አመትን በማሳለፍ በታሪኩ ዝቅተኛ የተባለው 8ኛ ደረጃ ይዞ ጨርሷል።

የእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ በመላው ዓለም በብዙ ሚሊዮን ተመልካችን ማግኘት የቻለ ጠንካራ የእግር ኳስ ፍልሚያ ሲሆን በሀገራችን #በኢትዮጵያም ሚሊዮኖች በተለይ ወጣቶች ውድድሩን ይከታተሉታል።

ቲክቫህ ስፖርት https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethiopia
#ስፖርት : ሪያል ማድሪድ በአውሮፓ ሻሚዮንስ ሊግ ፍጻሜ ቦሪስያ ዶርትመንድን በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነ።

ቡድኑ እጅግ ጠንካራ ነው የሚባለውን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በተደጋጋሚ አሸንፏል።

ቡድኑ በታሪኩ ይህን ዋንጫ ሲያሸንፍ 15ኛ ጊዜ ነው።

ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለይ በወጣቶች ዘንድ እንዲሁም በመላው ዓለም በርካታ ሚሊኒዮን ተመልካች ያለው ሲሆን ምርጥ የሚባሉት የአውሮፓ ክለቦች የሚሳተፉበት ነው።

Via @tikvahethsport

@tikvahethiopia
#ስፖርት #ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ።

ቡድኑ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ፍጻሜውን እስካገኘበት የሊጉ የመጨረሻ መርሃግብር ድረስ ከመቻል የእግር ኳስ ቡድን ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ነው ሻምፒዮን የሆነው።

ዛሬ በተካሄደ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድህንን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል።

በዓመቱ 64 ነጥብ በመሰብሰብም ከመቻል በ1 ነጥብ በልጦ አጠናቋል።

መቻል በዓመቱ የፍጻሜ መርሃግብር ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ተፋልሞ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም በ1 ነጥብ ተበልጦ ዋንጫውን ተነጥቋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በመጣበት አመት በታሪኩ የመጀመሪያው የሆነውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ ማሳካት ችሏል።

ቲክቫህ ስፖርት👇
https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport