TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ደላሎችም ይሁኑ ' ወደ ውጭ ሀገር እንልካችሏለን ' የሚሉ ኤጀንሲዎች የት እና ለምን ስራ እንደሚልኳቹ በደንብ አጣሩ !! ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ወጣቶችን " ለብሩህ ተስፋ፣ ለጥሩ ህይወት ጠቀም ያለ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ በታይላንድ አለ " በማለት ወጣቶቻችንን ለከፋ የስቃይ ህይወት የሚዳርጉ ሰዎች አሉ። አንዳንዶቹ ጭራሽ ወደ አሜሪካ ፣ ካንዳ እና አውሮፓ ሀገራት ነው የምንልካችሁ…
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#Myanmar

ይህ የ ' DW ዶክመንተሪ ' #በማይናማርና #ታይላንድ ድንበር ባሉ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰዎችን ከተለያዩ የዓለም ሀገራት በማዘዋወር ስለሚሰሩ ዓለም አቀፍ የኦንላይን ማጭበርበር (scam) ስራዎችን በግልጽ የሚያሳይ ነው።

የሰው አዘዋዋሪዎች ሰዎችን የሚያዘዋውሩት በቅድሚያ ታይላንድ / የአውሮፓ ሀገራት እንደሆነ በመግለጽ እና ጠቀም ያለ ገቢ እንደሚገኝ በመንገር ጭምር ነው በኋላ የሚሰራው ማጭበርበር (Online Scam) ነው።

ቦታዎቹ ብዙ ናቸው።

ልክ እንደ ካምፕ አይነት ሲሆኑ ከነዛም ውስጥ ብዙ እንግልት እና ስቃይ የሚደርስባቸው አሉ።

ገና እንደሄዱ ስልካቸውን የሚቀሙ ፣ ፍጹም ኢሰብዓዊ አያይዝ የሚያዙ፣ ካልሰሩ የሚደበደቡ ፣ ስቃይ የሚፈጸምባቸው አሉ።

ከነዚህ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ይገኙበታል።

አንድ ለቲክቫህ መልዕክቱን የላከ ወጣት በደረሰበት ድብደባ ለወራት ያህል በክራንች ለመሄድ መገደዱን ጠቁሟል።

በሌላ በኩል በዛው በማይናማር በስልክ ያነጋገርናቸው አንዳንድ ወጣቶች በማይናማርና ታይላንድ ድንበር የሚፈጸሙ ጉዳዮች ከአንድ ቦታ ሌላ ቦታ እንደሚለያዩ አስረድተው እነሱ በሚኖሩበት ምንም አይነት ስቃይ ይሁን ችግር ደርሶባቸው እንደማያውቅ ተናግረዋል።

ስልክም ሆነ ሌሎች አይነት ኤሌክትሮኒክስ ነገሮችን ተከልክለው እንደማያውቁ አስረድተዋል።

አሁንም የውጭ ፕሮሰስ ላይ ያላችሁ የት ሀገር ፣ በምን ስራ ዘርፍ እንደምትሄዱ በደንብ ጠይቁ።

በደላሎች ወደ ካናዳ ፣ አሜሪካ ፣ አውሮፓ ፣ ታይላንድ ጠቀም ያለ ገንዘብ ለሚያስገኝ ስራ እየተባሉ ብዙ ወጣቶች ዓለም አቀፍ የሆነ የኦንላይን የማጭበርበር (online scam) ስራ ወደ ሚሰራባቸው የማይናማር የተለያዩ አካባቢዎች ነው የሚወሰዱት።

ስቃይ ላይ ነን ስላሉት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ጉዳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ለማነጋገር ጥረት ያደርጋል።

ተጨማሪ ዶክመንተሪዎች እና ዓለም አቀፍ ዜናዎች ፦
Al Jazeera - Rebels uncover scam centers in Myanmar
DW Shift - Scam Factories in Myanmar
Sea Today - Indonesian Scam Victims
WION - 900 scam factory Chinese Victims rescued near Myanmar
CNN News18 - Mynamar Cyber Crimes
CCTV - Major Criminal Suspects Transferred to China from Myanamar

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia