TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#PretoriaAggrement

አሜሪካ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር እና በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤቪን ማሲንጋ ጋር ሆነው ወደ ትግራይ መቐለ ተጉዘው ከክልሉ ባለልስጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል።

አምባሳደር ሀመር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት አሜሪካ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር አሜሪካ ድጋፏን እንደምታደርግ ገልጸዋል።

የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ቀደመው ህይወት ለመመለስ ለተጀመረው ስራ 15 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደምታደርግም በይፋ አሳውቀዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ የአሜሪካ መንግስት የሰላም ሂደቱ እንዲቀጥል ፣ የፕሪቶሪያው ውል እንዲተገበር የሚያደርገውን ጥረት የሚደነቅ ቢሆንም ከዚህ በላይ አጠናክሮ መስራት አለበት ብለዋል። 

መቐለ የሄዱት አምባሳደር ማይክ ሃመር እና አምባሳደር ማሲንግ ከቀናት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ አቶ ጌታቸው ረዳን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ጋር በመሆን አግንኝተዋቸው መክረው ነበር።

#TikvahFamilyMekelle

@tikvahethiopia