TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Russia የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዙ፡፡ ፑቲን ከገቡበት የዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከምዕራባውያን ሃገራት ጋር ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ጦሩ በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንዲሆን ያዘዙት፡፡ ዛሬ ከከፍተኛ ባለስልጣናቶቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል የሆኑ…
#WW3

" ምዕራባውያን ሩስያን ወደ 3ኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ ነው " - የቤላሩስ ፕሬዜዳንት

የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ የምዕራባውያን ማዕቀቦችን " ሩሲያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ " ነው ሲሉ ተጠያቂ አድርገዋል።

#NATO ሀገራት ሩስያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፉ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንት ሉካሼንኮ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዝዳንቱ ምዕራባውያን ከማዕቀብ ጋር በተያያዘ እየሄዱበት ያለው መንገድ ከጦርነትም የከፋ ነው ያሉ ሲሆን ይህ ደግሞ ሩሲያን ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እየገፋ ነው ብለዋል።

ምዕራባውያን ከጽንፈኛ እርምጃዎቻቸው ወደኃላ ማለት ካልጀመሩ መጨረሻው ወደ #ኑክሌር_ግጭት ሊያመራ እንደሚችል ፕሬዜዳንቱ አስጠንቅቀዋል።

ይህ የቤላሩስ ፕሬዝዳንት ማስጠንቀቂያ የተሰማው የሩስያ አቻቸው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው #በከፍተኛ_ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን ካዘዙ በኃላ ነው።

@tikvahethiopia
#NATO

NATO ሩስያን ለማስቆም ወደ ዩክሬን የመግባት ሀሳብ እንደሌለው ገለፀ።

የNATO ዋና ፀሀፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ ሩሲያን ለማስቆም NATO በምድርም ሆነ በአየር ወደ ዩክሬን የመግባት ሀሳብ እንደሌለው ተናግረዋል።

ስቶልተንበርግ " የNATO ሃላፊነት ግጭቱ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይሆን፣ እንዳይባባስ ወይም በአውሮፓ ከNATO አጋሮች ጋር ወደ ሙሉ ጦርነት እንዳይቀየር ማረጋገጥ ነው " ሲሉ መናገራቸውን ኬዬቭ ኢንዲፔንደንት ፅፏል።

ከጦርነቱ ጋር ተያይዞ NATO የዩክሬንን ሰማይ ከበረራ ቀጠና ነፃ ሊያደርግ ይችላል የሚለውም ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ተነግሯል።

በሌላ በኩል የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በትላንትናው ዕለት የዩክሬን አየር ክልልን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ፥ ስዊድንን እና ፊንላንድን አስጠነቀቀች። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አስጠንቅቋል። አሁን በዩክሬን እና ሩስያ መካከል ያለው ጦርነት ተባብሶ በቀጠለበት ሁኔታ ሩስያ ፊንላንድ እና ስዊድንን ማስፈራራቷ ሌላ ዓለም አቀፋዊ ስጋት ፈጥሯል። የኃያላን ሀገራቱ ግብግብ በተለይ…
#NATO

NATO በዩክሬን እየተካሄደ ስላለው ጦርነት ሁሉንም መረጃዎች የቅርብ አጋሮቼ ናቸው ላላቸው ስዊድን እና ፊንላንድ እያካፈለ መሆኑን ዋና ጸሃፊው ጄንስ ስቶልተንበርግ ዛሬ አስታውቀዋል።

ስቶልተንበርግ ዛሬ በብራስልስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ “ለሩሲያ ወረራ ምላሽ ለመስጠት ከፊንላንድ እና ስዊድን ጋር ያለንን ትብብር እና የመረጃ ልውውጥ ለማጠናከር ወስነናል " ብለዋል።

አክለውም ፥ " ሁለቱም ሀገሮች አሁን ላይ ስለ ቀውሱ በሁሉም የNATO ምክክር እየተሳተፉ ነው። ” ሲሉ ተደምጠዋል።

ከቀናት በፊት ሩሲያ ፥ ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል #ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አጥብቃ ማስጠንቀቋ የሚዝነጋ አይደለም።

ሩስያ ሁለቱን ሀገራት አርፋችሁ ቁጭ በሉ ስትል ማስጠንቀቋ በዩክሬን ተባብሶ የቀጠለው ጦርነት ላይ ሌላ ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ስጋት እና አደጋ ሊፈጥር እንደሚችል ሲነገር እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ላይ ምንም እንኳን ሁለቱ ሀገራት የNATO አባል ባይሆኑም NATO ከሁለቱም ሀገራት ጋር ያለውን ገኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ወስኗል።

@tikvahethiopia
#UKRAINE #NATO

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ ዛሬ በመዲናቸው ኬዬቭ ሆነው በቴሌቪዥን ለህዝባቸው ባሰሙት ንግግር ላይ የተናገሩት ፦

" ...ምዕራባውያን መሪዎች ሩሲያ አገራችንን ልትወር መሆኗን ያውቁ ነበር፤ ፑቲን ከተሞቻችንን በቦምብ እንዲደበድቡ ፈቅደዋል።

በዩክሬን ላይ ጥቃት እንደሚፈጸም እና ጉዳትም የማይቀር መሆኑን እያወቀ NATO ሆን ብሎ የዩክሬን ሰማይ ለበረራ ዝግ እንዳይሆን አድርጓል።

የNATO መሪዎች ዛሬም ከበረራ ነጻ የሆነ ቀጠና ውሳኔን ባለማሳለፋቸው ምክንያት ተጨማሪ የዩክሬን ከተሞች እና መንደሮች በቦምብ እንዲደበደቡ ፈቅደዋል።

NATO ዩክሬንን ለመከላከል እርምጃ ባለመውሰዱ በጦርነቱ ምክንያት ለሚሞቱ የአገራችን ዜጎች ሕይወት ተጠያቂ ነው። "

ለምንድነው NATO የዩክሬንን አየር ማይዘጋው ?

NATO በምድርም ሆነ በአየር ወደ ዩክሬን የመግባት ፍላጎት የለውም።

ለNATO ውሳኔ ምዕራባውያን ባለሥልጣናት እንደምክንያት የሚያስቀምጡት በዩክሬን ከበረራ ነጻ የሆነ ቀጠና ከተከለለ የNATO አውሮፕላኖች ጥሰት በሚፈጽሙ የሩሲያ ተዋጊ አውሮፕላኖች ላይ ጥቃት መሰንዘር ይችላሉ።

ይህ ደግሞ 3ኛው የዓለም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።

@tikvahethiopia
#Update

ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ በዩክሬን የምታካሂደውን ወታደራዊ ኦፕሬሽን #ወዲያው እንደምታቆም አስታወቀች።

ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ፦

1ኛ. ወታደራዊ እርምጃ እንድታቆም።

2ኛ. ገለልተኛ አቋም እንድትይዝ ህገመንግስቷን እንድትቀይር (እንደ #NATO አይነት ጥምረት ውስጥ እንዳትገባ እንድታረጋግጥ)

3ኛ. ክሬሚያን እንደ ሩሲያ ግዛት እንድትቀበል።

4ኛ. የዶንቴስክ ​​እና የሉሀንስክ ተገንጣይ ሪፐብሊኮችን እንደ ነፃ ሀገር እንድትቀበል የሚሉት ናቸው።

እነዚህ ከተሟሉ ሩስያ ዩክሬን ውስጥ ምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ ወዲያውኑ እንደምታቆም ገልፃለች።

የክሬምሊን ቃልአቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በስልክ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ ዩክሬን ቅድመ ሁኔታዎቹን እንደምታውቅ እና ተፈፃሚ የሚሆኑ ከሆነ የወታደራዊ ዘመቻው ወዲያውኑ እንደሚቆም እንደተነገራት ገልፀዋል።

ከዩክሬን ወገን በኩል ወዲያው የተሰጠ ምላሽ የለም።

በሌላ በኩል ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሶስተኛው ዙር ድርድር ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ስውዲን እና ፊንላንድን የNATO አባል የማድረጉ ሂደት 'በፍጥነት' ይካሄዳል ብለን እንጠብቃለን " - የNATO ዋና ጸሐፊ ጄንስ ስቶለተንበርግ ከሩስያ ጋር 1300 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ድንበር የምትጋራው ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል የአባልነት ጥያቄዋን የፊታችን እሁድ ይፋ ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል። ስውዲንም የአባልነት ጥያቄዋን በተመሳሳይ ቀን ታቀርባለች ተብሎ ነው የሚጠበቀው።…
#NATO

ቱርክ ፤ የፊንላንድ እና ስውዲን NATOን መቀላቀል እንደማትደግፍ አስታወቀች።

የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፤ ሀገራቸው ስዊድን እና ፊንላንድን NATOን በአባልነት የመቀላቀል እቅድ እንደማትደግፍ ገልፀዋል።

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በግልፅ ባያብራሩም የኖርዲክ ሀገራት የብዙ አሸባሪ ድርጅቶች መገኛ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ዛሬ አንካራ ውስጥ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ኤርዶጋን ፥ " ስዊድን እና ፊንላንድን በሚመለከት ያለውን ሂደት እየተከታተልን ነው ፤ ነገር ግን በጉዳዩ ላይ አዎንታዊ አመለካከት የለንም " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም NATO ግሪክን በአባልነት መቀበሉ ስህተት ነበር ሲሉም ተደምጠዋል። " እንደ ቱርክ ተመሳሳይ ስህተቶችን መድገም አንፈልግም " ሲሉ አክለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በዝርዝር ባያብራሩም " የስካንዲኔቪያ አገሮች የአሸባሪ ድርጅቶች ማረፊያ ናቸው " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን ፤ " እንደውም በአንዳንድ ሀገራት የፓርላማ አባላት ናቸው ፤ እኛ ደጋፊ መሆን አንችልም (NATOን የመቀላቀል ጉዳይ) " ብለዋል።

ቱርክ ስውዲንን እና ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራትን አሸባሪ ስትል የፈረጀቻቸውን እንደ ኩርዲሽ ሚሊሻ ቡድን PKK እና YPG ፤ እንዲሁም በአሜሪካ መቀመጫቸውን ያደረጉትን የፈቱላህ ጉለንን ተከታዮች ይደግፋሉ/ያስተናግዳሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ይደመጣል።

አንካራ ጉሌኒስቶች እ.ኤ.አ. በ2016 መፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገዋል ስትል የምትከስ ሲሆን ጉለን እና ደጋፊዎቹ ክሱን አይቀበሉትም።

@tikvahethiopia
#Update

#ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO

➡️ የስዊድን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አን ሊንዴ ሀገራቸው የNATO አባል እንድትሆን ማመልከቻ መፈራረማቸው ተነግሯል። ሚኒስትሯ የፈረመት የአባልነት ጥያቄ ማማልከቻ ከፊንላንድ የNATO ማመልከቻ ጋር አብሮ ይቀርባል ሲሉ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

➡️ ዛሬ የፊንላንድ ፓርላማ የNATO ወታደራዊ ጥምረት አባል ለመሆን የቀረበውን ሀሳብ በ188 ድምጽ በስምንት ተቃውሞ አፅድቋል።

➡️ ፊንላንድ ለNATO አባልነት ማማልከቻ ልታቀር መሆኑን ተከትሎ ሩሲያ የኒኩሊየር ጦር መሳሪያ አስወንጫፊ ሚሳየሎችን ወደ ፊንላንድ ድንበር ማስጠጋቷ ተነግሯል ፤ ወደ ፊንላንድ ድንበር ያስጠጋ የኢስካንደር ሚሳየሎች እንደሆነ ተሰምቷል።

➡️ ስዊድን ለNATO አባልነት ጥያቄ ለማቅረብ ከውሳኔ ላይ መድረሷን ተከትሎ ሩሲያ በብሔራዊ ደህንነቷ ላይ የሚደርሰውን ስጋት ለመቅረፍ ወታደራዊ-ቴክኒካል እና ሌሎች የምላሽ እርምጃዎችን እንደምትወስድ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

➡️ የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በድጋሚ ሀገራቸው ፊንላንድ እና ስውዲን የNATO አባል ለመሆን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንደማይደግፉ አረጋግጠዋል። ሀገራቱ ወደ አንካራ የአግባቢ ልዑክ ይልካሉ እየተባለ ሲሆን ኤርዶጋን ግን " አቋማችን ግልፅ ነው ወደ አንካራ ልኡክ በመላክ ባትለፉ እኛንም ባታስቸግሩን ይሻላችኃል " ብለዋቸዋል።

ቱርክ ፤ ፊንላንድ እና ስውዲን የNATO አባል ለመሆን የሚያደርፉትን እንቅስቃሴ ለምንድነው የማትደግፈው ? ይህን ያንብቡ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/70164?single

መረጃዎቹ የተሰባሰቡት ፦ ከአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ ሲጂቲኤን ፣ ቴሌግራፍ፣ ኤፒ ፣ ዬል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO ➡️ የስዊድን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አን ሊንዴ ሀገራቸው የNATO አባል እንድትሆን ማመልከቻ መፈራረማቸው ተነግሯል። ሚኒስትሯ የፈረመት የአባልነት ጥያቄ ማማልከቻ ከፊንላንድ የNATO ማመልከቻ ጋር አብሮ ይቀርባል ሲሉ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል። ➡️ ዛሬ የፊንላንድ ፓርላማ የNATO ወታደራዊ ጥምረት አባል ለመሆን የቀረበውን ሀሳብ በ188 ድምጽ…
#Update

#ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO

➡️ ፊንላንድ እና ስዊድን NATOን ለመቀላቀል በይፋ የማመልከቻ ደብዳቤያቸውን ለNATO አስገብተዋል።

➡️ የNATO ዋና ፀሃፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ ፊንላንድ እና ስዊድን የዓለም ትልቁን ወታደራዊ ህብረት ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረባቸውን አረጋግጠዋል። ዋና ፀሀፊው 2ቱ ሀገራት የNATO አባል ለመሆን ያቀረቡትን ጥያቄ በከፍተኛ ደስታ መቀበላቸውን ገልፀዋል።

➡️ ፊንላንድ እና ስዊድን የNATO ጥምረት አባል ለመሆን ያቀረቡት ማመልከቻ በ30ዎቹ አባል አገራት የሚታይ ሲሆን ሂደቱ ሁለት ሳምንታትን ሊፈጅ እንደሚችል ተነግሯል። ቱርክ ሀገራቱን የአሸባሪዎች ማረፊያ ናቸው በማለት NATOን ለመቀላቀል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ደጋግማ መቃወሟ ይታወቃል።

➡️ ነገ ሀሙስ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን የስውዲን ጠቅላይ ሚኒስትር እና የፊንላንድ ፕሬዜዳንት በዋይትሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ፤ የ2ቱ ሀገራት መሪዎች NATOን ለመቀለቀል እያደረጉት ስለለው ሂደት ከባይደን ጋር ይወያያሉ ተብሏል። አሜሪካ ሀገረቱ የNATO አባል እንዲሆኑ ከፍተኛ ድጋፍን እየሰጠች ከምትገኝ ሀገር አንዷ ናት።

➡️ NATOን መቀላቀል በማሰቧ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሩስያ አሁንም ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን እያካሄደች ነው። ሩስያ
በዶኔትስክ እና ሉሃንስክ የምድር ላይ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች መቀጠሏ ተነግሯል።

➡️ ሩስያ፤ ፊንላንድና ስዊድን NATO የሚቀላቀሉ ከሆነ አፀፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ እየዛተች ነው ይህን ተከትሎ ፊንላንዳውያን በገፍ ወታደራዊ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ነው። እንደ ዩክሬን ልንወረር እንችላል በሚል የሃገሪቱን ጦር በመቀላቀል በፈቃደኝነት ወታደራዊ ስልጠናዎች እየወሰዱ ይገኛሉ።

#አልጀዚራ #አፒ #አልአይን #ቲአርቲ

@tikvahethiopia
ቱርክ #ኢትዮጵያም ያለችበትን የBRICS ስብሰብ ትቀላቀል ይሆን ?

ባለፈው ሳምንት የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የBRICS አባሏን ቻይናን ጎብኝተው ነበር።

በጉብኝታቸው ወቅት ከቻይና ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

በወቅቱ ሀገራቸው ቱርክ የBRICS ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተጠይቀው ፥ " በእርግጥም #እንፈልጋለን። ለምን አንፈልግም ? " ብለዋል።

" በእርግጥም ፤ የBRICS አባል መሆን እንፈልጋለን " ያሉት ፊዳን " ስለዚህ በዚህ አመት እንዴት እንደሚሄድ እናያለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ተጨማሪ ነገር ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

አናዱሉ እንደዘገበው ደግሞ ቱርክ የBRICS  አባላት ሀገራትን ትብብር እየተመለከተች ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊትም ወደ ሩስያ አቅንተው ከBRICS አባሏ ሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በዝግ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

በBRICS አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል።

ፑቲን ከሚኒስትሩ ጋር በነበራቸው ስብሰባ ቱርክ ስብስቡን ለመቀላቀል (አብሮ ለመስራት) ያሳየችውን ፍላጎት በደስታ ተቀብለው ፤ ወደ ስብስቡ እንድትቀላቀል ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

የቱርክ መንግሥት BRICS'ን ለመቀላቀል ርምጃ ይወስድ እንደሆነ እስካሁን የሚታወቅ ነገር የለም። ከዚህ ቀደም በይፋ ስብሰቡን ለመቀላቀል ያለውን ፍላጎት በይፋ አሳውቆ አያውቅም።

ቱርክ የ #NATO አባል ሀገር እንደሆነች ይታወቃል።

#BRICS+ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሩስያ ፣ የብራዚል ፣ የቻይና ፣ የህንድ ፣ የደቡብ አፍሪካ ፣ የኢራን ፣ የግብፅ ፣ የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ ስብስብ ነው።

#BRICS
#Turkey
#China
#Russia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቱርክ #ኢትዮጵያም ያለችበትን የBRICS ስብሰብ ትቀላቀል ይሆን ? ባለፈው ሳምንት የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የBRICS አባሏን ቻይናን ጎብኝተው ነበር። በጉብኝታቸው ወቅት ከቻይና ባለስልጣናት ጋር መክረዋል። በወቅቱ ሀገራቸው ቱርክ የBRICS ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተጠይቀው ፥ " በእርግጥም #እንፈልጋለን። ለምን አንፈልግም ? " ብለዋል። " በእርግጥም ፤ የBRICS…
#BRICS+

የNATO አባል ሀገሯ ቱርክ የBRICS አባል ለመሆን ይፋዊ ጥያቄ አቀረበች።

ቱርክ የBRICS አባል ለመሆን በይፋ ማመልከቻ ማቅረቧን የቱርክ ገዥ ፓርቲ ቃል አቀባይ ኦመር ሴሊክ አረጋግጠዋል።

ቃል አቀባዩ " ፕሬዝደንታችን የBRICS አባል መሆን እንደምንፈልግ ደጋግመው ተናግረዋል። ጉዳዩ በሂደት ላይ ነው " ብለዋል።

" በአባልነት ሂደት ላይ ያለውን እምርታ ለህዝብ እናሳውቃለን " ሲሉም ተናግረዋል።

ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የBRICS+ ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ማሳወቋ የሚዘነጋ አይደለም።

ቱርክ የ #NATO አባል ሀገር እንደሆነች ይታወቃል።

#BRICS+ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሩስያ ፣ የብራዚል ፣ የቻይና ፣ የህንድ ፣ የደቡብ አፍሪካ ፣ የኢራን ፣ የግብፅ ፣ የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ ስብስብ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia