TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቦነስ አይረስ🔝የአሜሪካው ፕሬዝደንት #ዶናልድ_ትረምፕ የአርጀንቲናዋ ዋና ከተማ ቦነስ አይረስ ለG- 20 ስብሰባ ሲደርሱ በአውሮፕላን ማረፊያው ተርሚናል ላይ #የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ አውሮፕላን ቆሞ ይታያል። ጠ/ሚር ዶክተር #አብይ በስብሰባው ላይ ይሳተፉ እንደሆን እስካሁን ግልፅ አልሆነም። ፕሬስ ሴክረታሪ #ቢለኔ_ስዩም ትናንት ስለጉዳዩ ተጠይቀው መልስ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

©Aeropuerto Internacional de Ezeiza - Ministro Pistarini (EZE)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

#የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ ለኢሳት ቴሌቭዥን ሙሉ ማስታወቂያ ሰጠ መባሉ #ሀሰት መሆኑን የድርጅቱ የኮሚኒኬሽን ሀላፊ አቶ አስራት በጋሻው ገልፀዋል።

"There is #fake and basless claim circulating about #ESAT media getting exclusive sponsorship from Ethiopian airlines. As a business organization Ethiopian airlines has the right to use any media outlet to advertise its product. So far ESAT didn't get any of this kind." -- Ethiopian Airlines Communications Head, Asrat Begashaw

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake Video‼️

በማህበራዊ ሚዲያ(በተለይም በfacebook) #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ ንብረት የሆነው #ቦይንግ_737 "ከመከስከሱ በፊት" ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘው #ቪድዮ_ሀሰተኛ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: ንብረትነቱ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ በኾነው ET 302 ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን የመከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ #ቻይናውያን_ወዳጆቻቸው ትላንት አደጋው በደረሰበት የሃማ ቁንጡሽሌ አካባቢ በመገኘት #ሐዘናቸውን ገልጠዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ሰብሰብ ብለው #ሲያለቅሱ ነበር። #የሌሎች_ሃገራት ሰዎችም በሥፍራው ነበሩ።

Via ዶቼ ቨለ
ፎቶ: ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EBOLA ጎማ ከተማ ውስጥ #ለመጀመሪያ ጊዜ የኢቦላ በሽታ መገኘቱ ዛሬ ተሰምቷል። በነገራችን ላይ #ጎማ ምስራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የምትገኝ ከተማ ስትሆን #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ በሳምንት 7 ጊዜ ወደ ከተማይቱ ይበራል።

Via ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ

በበረራ ቁጥር ET343 ላይ ስለነበረው ክስተት እና ከዛም ጋር ተያይዞ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ስለደረሱ ሪፖርቶች ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል።

አየር መንገዱ ምርመራውን አከናውኖ ሲጨርስ ምን እንደተፈጠረ በማረጋገጥ ተገቢውን የእርምት እርምጃ ይወስዳል ፤ እስከዛው የበረራ ሰራተኞቹ ታግደው ይቆያሉ።

በወቅቱ ምን እና እንዴት ተፈጠረ ? ስለሚለው በጉዳዩ ቀጥተኛ ባለቤት ከሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መስማት የሚያስፈልግ ሲሆን ምርመራ እንደተጠናቀቀ ጉዳዩን አየር መንገዱ ይገልፃል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በድፍን አፍሪካ አንጋፋና ቁጥር አንድ ፤ በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ ፣ በደህንነቱ መረጋገጥ እና በአገልግሎቱ ሁሉም የሚመርጠው ፤ የሀገርን ክብር ይዞ የሚንቀሳቀስ ሀገር የሚያስተዋውቅ፣ በርከት ያለ ሀብት የሚያስገባ የኢትዮጵያ ህዝብ አለኝ የሚለው ትልቁ እና ጠንካራው ተቋም ነው።

@tikvahethiopia
አዲስ አበባ 🛫 መቐለ !

#ከአዲስ_አበባ ወደ #መቐለ ከነገ ጀምሮ ዳግም በረራ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፥ " ተቋርጦ የነበረው ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ የአየር ትራንስፖርት በነገው ዕለት ይጀምራል " ብለዋል።

" በፌዴራል መንግስቱ እና በህወሓት መካከል የተደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የአቬየሽን ሰራተኞች ወደ መቐለ አቅንተው የመቐለ አየር መንገድ ለበረራ ምቹ ሁኔታ ላይ መሆኑን አረጋግጠዋል " ሲሉ አቶ መስፍን ገልፀዋል።

ነገ በሚጀምረው በረራ በቀን አንድ ጊዜ የሚካሄድ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የደንበኞችን ፍላጎትን መሰረት በማድረግ የበረራው ቁጥሩ ከፍ ሊል የሚችልበትን ሁኔታ እንደሚፈጠርም አሳውቀዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ ተቋርጦ የነበረውን የበረራ እንቅስቃሴ #በሁሉም የትግራይ ክልል የበረራ መዳረሻዎች ለማስጀመር ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም ዛሬ በሰጡት መግለጫ አንስተዋል፡፡

" ነገ የሚጀምረው በረራ (ወደ መቐለ) ከሌላው ወገኑ ጋር ግንኙነቱ ተቋርጦ የነበረውን የትግራይ ህዝብ ዳግም እንዲገናኝ ለማድረግ ትልቅ እድል የሚፈጥር " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ባለፈ የሸቀጦችና ሌሎች ተደራሽ የመሆን እጥረት የነበረባቸውን የሰብዓዊ ድጋፎችን በበቂ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ይህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን ከፍ ማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መሆኑንም ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡

#የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#Mekelle #AddisAbaba

• " ክልከላው ላይ የለንበትም ፤ መፍትሄ እንዲሰጥ ከፌደራል መንግስት እየተነጋገርን ነው " - የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች

• " ስለተባለው ነገር መረጃ የለኝም። እኛ የምናውቀው ነገር የለም። ... ለአየር መንገዱ ከመንግሥት በኩልም ቢሆን ምንም አይነት ክልከላን የሚመለከት መመሪያ አልተሰጠውም " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

• " ዝርዝሩን ለማወቅ እናጣራለን " - የፌዴራል ፖሊስ

ካለፉት ሶስት ቀናት ወዲህ ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ በሚደረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች በረራ ላይ በተለይም #ወጣት መንገደኞች እንዳይጓዙ ክልከላ ስለመኖሩ መንገደኞች እየገለፁ ይገኛሉ።

ትናንት ታህሳስ 30/2015 ዓ/ም ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ የአየር ቲኬት ቆርጠው አሉላ አባነጋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የተገኙት #በርካታ_ወጣቶች ጉዟቸው መሰረዙ ተሰምቷል።

መንገደኞች እንደሚሉት ከሆነ ክልከላው ከ16 ዓመት በላይ እና ከ64 ዓመት እድሜ በታች በተለይ ደግሞ ወጣቶችን ትኩረት ያደረገ ነው።

አንድ ቃሉን ለቢቢሲ የሰጠ መንገደኛ (የአዲስ አበባ ነዋሪ) ፤ " የልጆች እናት፣ የህክምና ሪፈር ያላቸው እና በእድሜ የገፉት ግን መሄድ እንደሚችሉ ነው የፌደራል ፖሊስ አባላቱ የነገሩን " ብሏል።

ይኸው መንገደኛ ፤ አዲስ አበባ ከተማ እንደሚኖር ፤ መታወቂያውም የአዲስ አበባ እንደሆነ ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ እንደሄደና አስፈላጊውን መረጃ እንዳረበ ነገር ግን ሊቀበሉት እንዳልቻሉ አመልክቷል።

የአየር መንገዱ ሠራተኞች ክልከላው ከቁጥጥራቸው ውጪ እንደሆነ ነግረውናልም ብሏል።

አንድ መንገደኛ ደግሞ አዲስ አበባ የሚያስተዳድረው ተቋም መኖሩን የሚገልፅ መረጃ ካሳየ በኃላ በረራ እንደተፈቀደለት ለቢቢሲ ተናግሯል።

ክልከላው ከመቐለ በተጨማሪም #በሽረ ኤርፖርትም ስለመኖሩ ተገልጿል።

ጉዳዩን በተመለከተ ማን ምን አለ ?

የትግራይ ክልልን እያስተዳደሩ ያሉ አካላት ፤ ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ (ትግራይ ቴሌቪዥን) በሰጡት ቃል በዚህ ክልከላ እንደሌሉበት እና የክልከላው እርምጃ በፌደራል መንግስት የተወሰደ እንደሆነ ገልፀዋል።

በጉዳዩ ዙርያ መፍትሄ እንዲሰጥ ከፌደራል መንግስት እየተነጋገረ መሆኑን አሳውቋል።

#የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ (ለቢቢሲ አማርኛ ክፍል) ፦

" ስለተባለው ነገር መረጃ የለኝም። እኛ የምናውቀው ነገር የለም።

እንደምታውቁት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእድሜና ጾታ ክልከላ የለውም። ምክንያቱም በሕግ እና በሥርዓት ነው የሚተዳደረው። እስከ ዛሬ እንዲህ አይነት ክልከላ የለንም። ወደ ድረ ገጻችን ብትገቡም ምንም አይነት ክልከላ እንደሌለ ታያላችሁ።

በተጨማሪም ለአየር መንገዱ ከመንግሥት በኩልም ቢሆን ምንም አይነት ክልከላን የሚመለከት መመሪያ አልተሰጠውም።

ምናልባት #የአካባቢው_መመዘኛ_ወጥቶ እንደሆነ የክልሉ ባለሥልጣናትን ብትጠይቁ የሚሻል ይመስለኛል።

በእኛ በኩል ግን እስካሁን የደረሰን ምንም አይነት መረጃ የለም። ከመንግሥት የተሰጠ ትዕዛዝም የለም። "

የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ (ለቢቢሲ አማርኛ ክፍል) ፦

" መረጃው የለኝም።

ተጓዦች በእድሜ ተለይተው በአውሮፕላን እንዳይጓዙ ተከልክለዋል የሚለውን መረጃ አሁን ከእናንተ ነው የምሰማው።

ዝርዝሩን ለማወቅ እናጣራለን። "

በጦርነት ምክንያት ለረጅም ወራት ያህል ተቋርጦ የነበረው ወደ መቐለ እና ሽረ እንደስላሴ የሚደረገው የመንገደኞች በረራ በቅርቡ ዳግም መጀመሩ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia