TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከግንቦት 15 እስከ 20/2014 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር ተያይዞ " ለደኅንነታቸው ጥበቃ እና በወንጀል ጥርጣሬ የሚፈለጉ ሰዎችን ለመለየት " በሚል ምክንያት ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች ፦ - ከአባላ - ከኮነባ - ከበረሃሌ…
#Afar

በአፋር ክልል በሰመራ ከተማ በሚገኝ የማቆያ ካምፕ ውስጥ #ያለፈቃዳቸው ተይዘው ከነበሩት የትግራይ ተወላጆች መካከል የተወሰኑት በአውቶብሶች እና የደረቅ ጭነት መኪኖች ተሳፍረው ወደ ቀደመ መኖሪያቸው እየተወሰዱ እንደሆነ መግለፃቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።

በሺዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ተወላጆች ከአፋሯ አብኣላ ተይዘው ወደ ሰመራ ተዘዋውረው የነበረ ሲሆን  ከ8 ወራት እስር በኋላ ወደ አብኣላ እየተመሰሉ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰመራ ተይዘው የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን "በብሔር ማንነት ላይ የተመሰረተ ሕገ ወጥ እና የዘፈቀደ እስር በመሆኑ በአፋጣኝ ሊለቀቁ ይገባል ብሎ ነበር።

https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/71528?single

የትግራይ ተወላጆቹ ቀደሞ ወደሚኖሩበት የመኖሪያ ስፍራቸው እንዲመለሱ እያመቻች የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት (OCHA Ethiopia) መሆኑ የተነገረ ሲሆን ድርጅቱ ሰዎቹን " የአገር ውስጥ ተፈናቃይ (IDP) " ሲል ገልጿቸዋል።

ዜጎችን ወደነበሩበት ቦታ የመመለሱ ስራ በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚቀጥልም ገልጿል።

ነገር ግን ተመድ ባሰራጨው መረጃ ላይ በርካቶች በቃል አጠቃቀሙ ላይ ያለቸውን ተቃውሞ የገለፁ ሲሆን እነዚህ ተይዘው የነበሩት ዜጎች " ያለአንዳች ፍላጎታቸው በመውሰድ ነው " እንጂ የውሥጥ ተፈናቃይ አይደሉም ብለዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩት እዚህ ዜጎች ለወራት ተይዘው በቆዩበት ካምፕ ውስጥ የምግብ እና ሌሎች አገልግሎቶች ችግሮች እንደነበሩባቸው የተናገሩ ሲሆን ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋልጠው መቆየታቸውን እንደገለፁለት ቢቢሲ አስነብቧል።

@tikvahethiopia