TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ 'በወሰን ይገባኛል' ጥያቄ የተነሳው ግጭት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ታማኝ ምንጭ፣ " ግጭቱ ወደ ገጠሩ የመዛመት ሁኔታ ነው የሚስተዋለው። ወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ  ካልሆነ በቀር የከፋ ነገር የለም " ብለዋል። ወሸርቤ፣ ወልቂጤ ዙሪያ ግጭቱ መዛመት አዝማሚያ ያንዣበበባቸው የገጠር ቦታዎች…
#Update

የጊዜያዊ ኮማንድ ፓስት በወልቂጤ ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዳይገባ እና ወደ መደበኛ ስራው እንዳይመለስ እያደረጉ ነው ያላቸውን ህገ-ወጥ ግለሰቦችን አስጠነቀቀ።

ኮማንድ ፖስቱ ፤ በየቦታው የተለያዩ ትንኮሳዎችን በመፍጠር የከተማው ማህበረሰብ እንዳይረጋጋ እያደረጉ ነው ያላቸውን በስም ጠርቶ ያልገለፃቸውን አካላት በጥብቅ አስጠንቅቋል።

በተጨማሪ ፤ በተሽከርካሪና በእግር የሚንቀሳቀሱ ዜጎች ላይ ህገ-ወጥ ድርጊት እየተፈጸመ እንደሆነ ገልጾ " ይህ መቆም መቻል አለበት " ብሏል። የሚፈፀመውን ድርጊት እንዲሁም ስለፈፃሚዎች በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ይህን ማስጠንቀዊያ ሳይቀበል ወይም ተግባራዊ ሳያደርግ ቀርቶ በህገ-ወጥ ድርጊት የሚሳተፍ የየመዋቅሩ #የቀበሌ_አመራርና ግለሰብ በጸጥታው አካሉ ለሚወሰድበት #እርምጃ ኮማንድ ፖስጡ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን በጥብቅ አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን በወልቃጤ ከተማ በተፈጠረ ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱ፣ ንብረትም መወደሙ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia