TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar 15ኛው የአፋር ሱልጣን በዓለሲመት ሰኞ ይከናወናል። የፊታችን ሰኞ መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ሱልጣን አህመድ አሊሚራሕ  15ተኛው የአፋር ሱልጣን በመሆን  በዓለሲመታቸው እንደሚከናወን የአፋር ማስ ሚዲያ ኤጀንሲ ዘግቧል። ለዚሁ በዓለሲመት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ ዛሬ አዲስ አበባ  ገብተዋል። አዲስ አበባ ሲገቡ ከፍተኛ  አመራሮች ተገኝተው  አቀባበል አድርገውላቸዋል። @tikvahethiopia
#Afar

ቀጣይ የአውሳ ሱልጣኔት አልጋወራሽ እንደሚሆኑ የሚጠበቁት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ በዓለሲመታቸዉን ለመከወን ዛሬ  የአፋር መዲና፣ ሰመራ መግባታቸውን የአፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።
   
ሱልጣን አህመድ አልሚራህ ሰመራ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመሬሮችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች አቀባባል አድርገዉላቸዋል።

በዓለሲመቱ የሰኞ መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ/ም በአውሳ ሱስለጣኔት መናገሻ በሆነችው አይሳኢታ ከተማ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከናወን ይጠበቃል።

በእለቱ ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከሚገኙ እና በጀቡቲና ኤርትራ የሚገኙ የአፋር ማህበረሰብ ባህላዊ መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸዉ ሰዎች እንዲሁም የፌድራልና የክልሉ መንግስት አካላት አምባሳደሮች እንደሚገኙ ይጠበቃል ተብሏል።

#አፋብመድ

@tikvahethiopia