TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሰቦት

" የገዳማውያኑን የእርዳታ ጥሪ በተጠንቀቅ ጠብቁ " - አባ ገ/ሚካኤል

በአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴ ወአባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም አካባቢ በከፍተኛ ደረጃ የሰደድ እሳት የተነሳ ሲሆን ከትላንት ምሽት ጀምሮ ግን ወደ ገዳሙ በከፍተኛ ሁኔታ #እየተጠጋ እንደሆነና እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል።

አባ ገ/ሚካኤል የተባሉ የገዳሙ አገልጋይ ለተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል በሰጡት ቃል ፤ የእሳት ቃጠሎ መነሻው በሥርዓት ያልታወቀና የሰደድ እሳት እንደሆነ ገልጸዋል።

ከ3 ዓመታት በፊት ከፍተኛ እሳት ተከስቶ ለዘመናት የኖሩ የገዳሙን ብርቅዬ አራዊትና ደን ማውደሙን አስታውሰዋል።

በአሁኑ ሰዓት እሳቱን ለመቆጣጠር ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው ፤ የእሳቱ አደጋ የሚከፋ ከሆነና መቆጣጠር ካልተቻለ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የገዳማውያኑን የእርዳታ ጥሪ በተጠንቀቅ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል።

#Update

እሳቱ ለገዳሙ እንደማያሰጋ ተገልጿል።


#ተሚማ
@tikvahethiopia