TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት

ከንጋቱ 11:30 አንስቶ የሚዘጉ መንገዶች !

ነገ በአዲስ አበባ ፤ በኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ አማካኝነት የተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ይካሄዳል።

ሩጫው መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ ሲሆን ውድድሩ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ፦

- ከቅዱስ ዑራኤል ቤተ-ክርስቲያን  ወደ መስቀል አደባባይ
- ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከአጎና ሲኒማ  ወደ መስቀል አደባባይ
- በወንጌላዊት ህንፃ ወደ ጎተራ
- ከዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጎተራ
- ከጎፋ ገብርኤል ወደ ጎፋ ማዞሪያ
- ከሳር ቤት ወደ ጎፋ ማዞሪያ
- ከአፍሪካ ህብረት ወደ ብልጋሪያ
- ከትንባሆ ሞኖፖል ወደ ገነት ሆቴል
- ከጥይት ቤት ወደ ጠማማው ፎቅ
- ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር
- ከልደታ ቤተ ክርስቲያን ወደ ለገሃር
- ከሰንጋ ተራ ወደ ለገሃር
- ከብሔራዊ ቴአትር ወደ ለገሃር
- ከሐራምቤ ሆቴል  ወደ መስቀል
- ከቤተመንግስት ወደ መስቀል
- ከካዛኝቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

በውድድር መስመር  ግራ እና ቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው።

የሩጫው ተሳታፊዎች ፀጥታው የጋራ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ወደ መሮጫ ስፍራ ሲገቡ #ለፍተሻ እንዲተባበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ  ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢፍጧር የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል። በነገው ዕለት በአዲስ አበባ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመስቀል አደባባይ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርኃ ግብር  ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት፡- - ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን - ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ   ኦሎምፒያ…
#ATTENTION

ሁሉም ምዕመናን ወደ ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጧር በኢትዮጵያ-4 ሲመጡ ሊከተሏቸው የሚገቡ ደንቦች የሚከተሉት ናቸው።

1ኛ. ለጸጥታ አካላትና ለበጎ ፍቃድ አስተባባሪዎች #ለፍተሻ ትብብር ማድረግ ይገባል።

2ኛ. የሰላት መስገጃ እና ጥላ ይዘው መምጣት እንዳይዘነጉ።

3ኛ. ለማፍጠሪያ የሚሆንና ሙስሊም እህትና ወንድሞችን በማካፈል ኢፍጣርን ለሌሎች በማጋርት የሚገኘውን አጅር ተቋዳሽ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል። ምግቦቹ እንደ ፦
- ቴምር፣
- ውሃ
- የታሸጉ ምግቦች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

4ኛ. ማንኛውም ለደህንነት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፍቃደኛ አስተባባሪዎችና ለጸጥታ አካላት በአፋጣኝ ማሳወቅ ይገባል።

5ኛ. ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግጅት ዋናው ዓላማ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከሌሎች ጋር ኢፍጣርን በማጋራት የሚገኘውን አጅርና ደስታ እንዲያጣጥም ከማስቻል ባሻገር ሙስሊሞች ምንም ዓይነት ልዩነት ሳይገድባቸው ህብር ብሄራዊ  አንድነታቸውን በማሳየት ለሃገር ሰላምና ዕድገት በጋራ አላህን የሚማፀኑበት ዝግጅት ስለሆነ ከዝግጅቱ ዓላማ ውጪ ከሆኑ ድርጊቶች በመቆጠብ ኢስላማዊ ስነምግባርን ለሌሎች ዓርኣያ በመሆን ማሳየት ይገባል።

6ኛ. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለተፈናቀሉ ወገኖችን ድጋፍ ስለሚሰበሰብ ከወዲሁ በረመዳን ለተቸገሩ ድጋፍ በማድረግ የሚገኘውን ታላቅ አጅር እንዲሸምቱ ጥሪ ተላልፏል።

7ኛ. የዝግጅቱ አላማ መዓድ መጋራት እንደመሆኑ ከአላሰፈላጊ የምግብ ብክነት በመቆጠብ ምዕመኑ ሃይማኖታዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

8ኛ. ንፅህና የሙስሊም መገለጫ እንደመሆኑ ሁሉም ምዕመን የተጠቀመባቸው እቃዎች በአግባቡ እንዲያስወግዱ።

(ከአዘጋጆቹ ሀላል ፕሮሞሽን እና ነጃሺ በጎ አድራጎት ድርጅት)

ከ5:00 ሰዓት ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች 👇
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/86345

@tikvahethiopia