TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ?

በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።

አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።

ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።

በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።

ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።

በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።

ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።

ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።

የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።

በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።

ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።

የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል  ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።

#ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia