TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃለማርያም ሀገር ጥለው ከወጡ ዛሬ ድፍን 33 ዓመት ሆኗቸዋል። የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪ ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ/ም ነው ከሀገር የወጡት። የድርግ ውድቀትን እና የ #ኢህአዴግ ወደ አዲስ አበባ መቃረብን ተከትሎ ከሀገር እንደወጡ የሚነገርላቸው ኮ/ሌ መንግሥቱ ኃለማርያም በአንድ ወቅት ፤ " እኔ ኮብልዬ አልወጣሁም " ሲሉ ነበር ቃላቸውን…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮጵያ #ታሪክ

የቀድሞው ፕሬዜዳንት ሀገር ጥለው ከወጡ በኃላ ለ7 ቀናት ኢትዮጵያን ያስተዳደሩት ሌ/ጀነራል ተስፋዬ ገ/ኪዳን ናቸው።

የ7 ቀኑ መንግሥት በወቅቱ ' የተስፋዬዎች መንግስት ' የሚል ስም ተሰጥቶት ነበር። ይህ ስያሜ የተሰጠው ፦

- ተስፋዬ ገ/ ኪዳን ➡️ ተጠባባቂ ፕሬዜዳንት
- ተስፋዬ ዲንቃ ➡️ ጠቅላይ ሚኒስትር
- ተስፋዬ ወልደስላሴ ➡️ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር
- ተስፋዬ ታደሰ ➡️ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው ነው።

ሌ/ጄነራል ተስፋዬ በተለይም ፦

" #የኢትዮጵያ_ህዝብ_ሰላም_ጠምቶታል። የችግሮች ሁሉ ምንጭ የሰላም መታጣት በመሆኑ ቀዳሚው ጉጉቱና ናፍቆቱ ሰላም ነው።

በሰሜንም ሆነ በደቡብ፣ በምስራቅም ሆነ በምዕራብ በመሃልም ሆነ በደንበር ኢትዮጵያዊ እናት፣ ኢትዮጵያዊ አባት፣ የወደፊት ባለተስፋ የሆነው ወጣት ሁሉ ከምን ጊዜ በላይ ምኞቱ ሰላም ነው። " በሚለው ንግግራቸው ይታወሳሉ።

ከ7 ቀናት የ ' ተስፋዬዎች መንግሥት ' በኃላ ኢህአዴግ ሀገሪቷን ተቆጣጠረ ፤ 17 ዓመታትን በስልጣን ላይ የቆየው ደርግም እስከወዲያኛው ላይመለስ አከተመ።

#ኢትዮጵያ #Ethiopia
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia