TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ት.ዲ.ት.ፓ.‼️

መንግስት የራያ ህዝብ እያቀረበ ያለውን የማንነት ጥያቄ ህገመንግስቱን ማዕከል በማድረግ #አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ፓርቲ ጠየቀ፡፡ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ኢንጅነር ግደይ ዘርዓፅዮን እንደተናገሩት፤ በትግራይና በአማራ ክልል ውስጥ ያሉ አንዳንድ የፖለቲካ አመራሮች ለግል ጥቅማቸው ሲሉ በሚነዙት የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ምክንያት የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ምላሽ አጥቷል፡፡

በዚህም የህዝቡ ደህንነት አደጋ ላይ የወደቀ በመሆኑ መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡ በህዝቡ የተነሳውን ጥያቄ ሁለቱ ክልሎች ተመካክረው ሊፈቱት ይገባ የነበረ ቢሆንም ለጉዳዩ በቂ ትኩረት ባለመስጠታቸው ምክንያት አንዱ ክልል በሌላው ላይ መንገድ እስከመዝጋት
የሚደርስ ተግባር የሚፈፀምበት ሁኔታ መኖሩን ምክትል ሊቀመንበሩ አመልክተዋል፡፡

"ፓርቲያችን በሁለቱም ክልሎች በየጎዳናው የሚደረገው ዛቻና ፉከራ ለማንም ይጠቅማል ብሎ አያምንም" ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ የራያ ህዝብ ጥያቄ በህገመንግስቱ መሰረት ወደ ፈዴሬሽን ምክር ቤት መጥቶ በህግ አግባብ ውሳኔ መሰጠት ይኖርበታል ብለዋል፡፡ "እኛ አሁን የምንጠይቀውና ጫና የምናደርገው የትግራይ ክልል መንግስትን ነው" ያሉት ምክትል ሊቀ መንበሩ ጉዳዩ በሌላ አካል ባይቀርብም እንኳ የክልሉ መንግስት ራሱ ለፌዴራል መንግስት ጥያቄ በማቅረብ እልባት እንዲያገኝ ማድረግ የሚጠበቅበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ሊቀ መንበሩ የሁለቱም ክልል አመራሮች በህዝቦች መካከል ቅራኔ የሚፈጥሩ ትንኮሳዎችን በመከላከል የአገር ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተመራቂዎቹ ጥያቄ....

"ሰላም ፀግሽ ...ዶክተር ሳ__ እንባላለሁ ከመቀለ ዩኒቨርሲቲ የካቲት 16 ነበር የተመረቅኩት እስካሁን ስራ አልመደቡንም፤ ከዚህ በፊት ከሁለት ሳምንት በኃላ ነበር የሚመድቡት #FOMH አናግረን ነበር እናም ሁሉም ክልል ለሀኪም የሚሆን #በጀት_የለንም ብለዋል፤ ጠብቁ የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን። 7 አመታትን በአድካሚ የትምህርት ስርዓት አልፈን ይህ መሆኑ አሳዝኖኛል።"

ይህን መሰሉ በርካታ ተመሳሳይ መልዕክቶች እየመጡ ናቸው፤ ተመራቂ ዶክተሮቹ መንግስት #አፋጣኝ_ምላሽ እና #መፍትሄ እንዲፈልግላቸው እየጠየቁ ናቸው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማኅብረቅዱሳን በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። የሁለቱም አገልጋዮች የመኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል…
#Update

የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉኅን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ ትላንት በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚገኙ ተገልጾ ነበር።

ዛሬ ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ማኅበረ ቅዱሳን አሳውቋል።

ምንም እንኳን አመራሮቹ በምን ምክንያት ተይዘው እነደነበር  ያብራራው ነገር ባይኖርም ፥ " በሂደቱ ጉዳዩን በመረዳት #አፋጣኝ_ምላሽ የሰጡንን የመንግሥት የጸጥታ አካላት እናመሰግናለን " ብሏል።

@tikvahethiopia