TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለመከላከያ ሰራዊት‼️

#አላማጣ ላይ በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት ጠፍቷል። ከባድና ቀላል ጉዳትም ደርሷል። ነዋሪዎች መከላከያ ገብቶ ችግሩን እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update

• ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው ኔትዎርክ ጀምሯል ፤ አላማጣና ኮረም በሰዓታት ውስጥ አገልግሎት ያገኛሉ።

ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው የኔትዎርክ አገልግሎት ጀመረ።

የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ፤ የኔትዎርክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩት ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው ዳግም የኔትዎርክ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ዛሬ ገልፀዋል።

የጄኔሬተር ነዳጅ ወደ አካባቢው በመላክ #አላማጣ እና #ኮረም ከሰዓታት በኋላ ሙሉ ለሙሉ የኔትዎርክ አገልግሎት እንደሚያገኙ ገልፀዋል።

በጥገና እና የተጎዱ የቴሌ መሠረተ ልማቶችን በመተካት ከዚህ ቀደም አገልግሎት ካገኙ አካባቢዎች ባለፈ በሌሎች የኔትዎርክ አገልግሎት የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በቅርቡ አገልግሎት ለማስጀመር በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ መናገራቸውን ኢብኮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ተፈናቃዮችን ወደ ቤታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ነው ፤ ይህም ይቀጥላል " - የብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት

የብሔራዉ የደኅንነት ምክር ቤት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ባጋጠመ ግጭት፤ እንዲሁም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ባጋጠሙ የጸጥታ ችግሮች የተነሣ የተፈናቀሉ ዜጎች እንዳሉ ገልጿል።

" እነዚህ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ እየሠራን ነው " ብሏል።

" የአማራ እና የኦሮሚያ ክልል አመራሮች በጋራ ሠርተው ብዙዎችን ከመጠለያ ጣቢያ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ተደርጓል " ሲልም ገልጿል።

" በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል፤ #በራያ እና #አላማጣ አካባቢ ከተፈናቀሉ ዜጎች መንግሥትን ሳይጠብቁ በማኅበረሰባዊ መተሳሰብ ብቻ በርካታዎች ወደ ቤታቸው እየገቡ ነው " ሲል አመልክቷል።

በዚህ ሂደት " የተፈናቃዮችን ጉዳይ እንደ ፖለቲካ አጀንዳ አድርገው ሊጠቀሙ የሚፈልጉ አካላት መኖራቸው ታይቷል " ብሏል።

ም/ቤቱ እነዚህ ኃይሎች እነማን እንደሆኑ በግልጽ በስም ጠርቶ ባይገልጽም " ተፈናቃዮቹ ወደ ቤታቸው እንዳይመለሱ ፕሮፖጋንዳና ማስፈራሪያ ይደረድራሉ " ብሏል።

" አንዳንዴም #በኃይል ጭምር የተፈናቃዮችን መመለስ ለማሰናከል ይቃጣቸዋል። " ሲል ገልጿል።

" መንግሥት ካለበት የሞራል እና የሕግ ኃላፊነት የተነሣ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቤታቸውና ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ማድረጉን ይቀጥላል " ሲል አሳውቋል።

https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/87168?single

@tikvahethiopia