TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ድሬ ፖሊስ‼️

#ብሄሬን መሰረት ተደርጎ ጥቃት ተፈፅሞብኛል በሚል በሀሰት የሽንት መሽኛ #ብልቱን በፋሻና ፕላስተር በመጠቅለል ግጭት ለመቀስቀስ የሞከረው ግለስብ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ተጠርጣሪ #ኢብራሂም_ደደፎ_አብደላ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስበት ሆን ብሎ ብሄሬን መሰረት አድርገው በቢላዋ የሽንት መሽኛ ብልቴን ቆርጠው ጉዳት አድርሰውብኛል በሚል ድርጊቱን ያልፈፀሙ ግለሰቦችን ስም በመጥቀስ ለፖሊስ አቤቱታ ያቀረበው።

ፖሊስ የቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ሁኔታውን ለማጣራት ተከሳሽን ወደ ህክምና የላከ ሲሆን በተደረገ የህክምና ምርመራ ግለሰቡ ላይ ምንም አይነት ጥቃት #እንዳልተፈፀመበት ማረጋገጥ መቻሉን ተናግሯል።

#ተጠርጣሪው አሁን ላይ #በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ ጨምሮ ገልፆ ማንኛውም ሰው በዜጎች መካከል ግጭቶችና አለመግባባቶች እንዲፈጠሩ ከሚያደርጉ ተግባራት ሊቆጠብና ሊርቅ እንደሚገባ አሳስቧል::

ምንጭ፦ ድሬ ፖሊስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሸዋሮቢት‼️

በሸዋሮቢት ከተማ የተከሰተው አለመረጋጋት ከተፈጸመው #አሰቃቂ_ግደያ ጋር ተያይዞ ማህበረሰቡ ብሶቱን ለመግለጽ እንጂ ከየትኛውም #የፖለቲካ ጉዳይ ጋር የተያያዘ አለመሆኑን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር #ሞገስ_ባየህ ለአማራ ብሁሃን መገናኛ ለ91.4FM በስልክ በሰጠው መግለጫ አስታውቀዋል።

የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ለ91.4 FM እንዳገለጹት #ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሏል አስፈላጊውን የምርመራ ስራ ተሰርቶና ተጣርቶ ህጋዊ #እርምጃ እንዲወሰድ ይደረጋል ውጤቱንም ለህዝብ እናሳውቃለን ህብረተሰቡ ከስሜታዊነት ወጥቶ በተረጋጋ መንግድ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል።

እንደ ሀላፊው ገለጻ ከአካባቢው የሀይማኖት አባቶች፣ ሀገር ሽማግሌዎች እና ከከተማው ህብረተሰብ ጋር በመከካከር ወደ ነበረበት ሰላም ለመመለስ የምክክር ስራ ይሰራል ብለዋል። አሁን ከህብረተሰቡ የሚጠበቀው በሰላም ወደ እየቤቱ መመለስ እንዳለበት የተዘጉ መንገዶችን ከፍቶ መንገደኞችን #መሸኘት እንደለበት አሳስበው ድርጊቱ ግን ብሶትን /ቁጭትን/ ለመግለጽ እንጂ #የፖለቲካ_አጀንዳ እንደሌለው ሀላፊው ተናግረዋል። የጸጥታ ሀይሉም ጉዳዩ በህግና በህግ እንዲያልቅ የማረጋጋት ስራ እየሰራ ነው።

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia