TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SolveITAccelerator

Icog Labs ከJICA ጋር በመተባበር ከኩዱ ቬንቸር በተገኘ ድጋፍ Solve IT Accelerator በተሰኘ ፕሮግራማቸው ለሥራ ፈጣሪዎችን ለማብቃት ፣ የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም የተለያዩ ስልጠናዎችንና ድጋፎችን ለማድረግ መጨረሳቸውን አዘጋጆቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Solve IT Accelerator በቅርቡ በይፋ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ሲሆን ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን የሚመዘግብበትና ስለ ፕሮግራሙ የሚገልጽበትን ድረ ገጽ ይፋ አድርጓል፡፡ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቤተሰቦቻችን ይህንን እድል እንዲትጠቀሙ እየጠቆምን ተከታታይ መረጃዎችንም የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

More http://www.icog-sa.com

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaB
#SolveITAccelerator

5 ሚሊዮን ብር ለሥራ ጀማሪዎች ማጠናከሪያ!

iCog labs,JICA ከኩዱ ቬንቸር በተገኘው የ5,000,000 ብር [አምስት ሚሊዮን ብር] የገንዘብ ድጋፍ ሥራ ላይ ያሉ እና ምርትና አገልግሎታቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ላይ ለተሰማሩ ሰባት ድርጅቶች የአቅም ማበልጸግ ፣ የገበያ ትስስር መፍጠር እና በትንሹ 250,000 ብር ከፍ ካለ እንደ ፕሮጀክቱ ታይቶ የሚጨመር ድጋፍ ለመስጠት ጀምሯል።

የፕሮጀክቱ ማናጀር የሆኑት አቶ ህሩይ ፀጋዬ እንደገለጹት ሥራ ጀማሪዎቹ ከፕሮግራሙ ጋር በሚኖራቸው ቆይታ ማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ፕላናቸውን ይበልጥ እንዲያሻሽሉ የሚደረግ ይሆናል።

ከ7ቱ ፕሮጀክቶች መካከል 5ቱን በመውሰድ 10 ቀን የሚቆይ የውጭ ሀገር ልምድ ልውውጥ እና የሚያስፈልጋቸው የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ገበያው እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል፡፡

"ይህንን መሰሉን ሥራ ስንሰራ በዋናነት ማወቅ የምንፈልገው የቴክኖሎጂው ዘርፍ በኢትዮጵያ ምን አይነት ደረጃ ላይ ደርሷል የሚለውን ነው" ያሉት አቶ ህሩይ "የወጣቱን አቅም ማጎልበትና ትርፋማ ማድረግም ሌላው ትኩረት የምንሰጠው ጉዳይ ነው" ብለዋል፡፡

በዚህ ስራ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ፣ የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲና ጥቃቅ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በአጋርነት ይሰራሉ ተብሏል፡፡

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia