TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ

° በኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ህጻናት መደበኛ ክትባት ወስደው አያቁም።

° የአለም የህጻናት አድን ድርጅት ከክትባት ጋር የተያያዘ ችግሮችን የሚፈቱ የፈጠራ ስራዎችን እያወዳረ ነው።


አፍሪካ በዓለም ' ዜሮ ዶዝ ' ህፃናት ከሚገኙባቸው አህጉራት በቁጥር ከፍተኛውን ደረጃ ትይዛለች። ይህም ማለት መደበኛ ክትባት ወስደው የማያውቁ 8.7 ሚሊዮን ህፃናቶች አሉ ማለት ነው፡፡

ከእነዚህ ህፃናት ውስጥ ከአንድ ሦስተኛ በላይ የሚሆኑት የሚኖሩት በናይጄሪያ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ህጻናት መደበኛ ክትባት ወስደው አያቁም።

በተጨማሪም ወረርሽኝ ፣ ድህነት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ፣ አለመረጋጋት፣ ግጭቶችናና ተያያዥ ምክንያቶች የክትባት መርሃግብሮችን እየተስተጓጎሉ ይገኛሉ።

የዓለም የህጻናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) እና ጂኤስኬ በመተባበር የክትባት አቅርቦትን እና አጠቃቀምን በተመለከተ ማንኛውንም አይነት ከክትባት ጋር የተያያዘ ችግሮችን የሚፈቱ የፈጠራ ስራዎችን በማወዳደር ላይ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጠቅሷል።

የተመረጡ ኃሳቦች / ሥራዎች በፕሮጀክት እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ የገንዝብ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።

ለማመልከት www.stc-accelerator.org ይጎብኙ።

የማመልከቻ ቀን እስከ #ግንቦት_16 ቀን 2016 ዓም ድረስ ነው።

ሁለተኛው የፈጠራ ጥሪ በ2017/2025 የሚካሄድ ይሆናል።

@tikvahethiopia