TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MoH

የጤና ባለሞያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ከታህሳስ 21 እስከ ታህሳስ 27 ድረስ ይሰጣል።

በህክምና ፣ ነርሲንግ ፣ ጤና መኮንን ፣ ፋርማሲ ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ቴክኖሎጂ፣ ሚድዋይፈሪ፣ አንስቴዥያ፣ ዴንታል ሜድስን እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ ሙያዎች ተመርቀው የጤና ሚኒስቴር የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ለተመዘገቡ የጤና ባለሙያዎች ፈተናው የሚሰጠው ከታህሳስ 21-27/2014 ዓ.ም ድረስ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፥ ተፈታኞች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቦ የፈተናውን ፕሮግራም በቅርብ ቀን እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#MoH

የጤና ተቋማት ወደነበሩበት ለመመለስ ርብርብር እየተደረገ ነው።

በግጭት ምክንያት የወደሙና የተጎዱ ጤና ተቋማትን ወደነበሩበት ለመመለስ እና የጤና አገልግሎት ለማስጀመር የአዲስ አበባ ጤና ቢሮና የፌዴራል ሆስፒታሎችን ከወደሙ ሆስፒታሎች ጋር በማስተሳሰር ድጋፍ እንዲያደርጉ ሰፊ ስራ መጀመሩን ከጤና ሚኒስቴር ተሰምቷል።

በቀጣይ ሌሎች ክልሎች እና ዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎችን በማስተባበር የድጋፍ ስራው በስፋት እንዲቀጥል ይደረጋል ተብሏል።

በአሁኑ ሰዓት:-

• ቅዱስ ጳውሎስ ሚሌንየም ሜዲካል ኮሌጅ 👉 ደሴ ሆስፒታልን፤
• ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 👉 ከልዋን ሆስፒታልና ቦሩ ሜዳ ሆስፒታልን፤
• አቤት ሆስፒታል 👉 ባቲ ሆስፒታልን፤
• የካቲት 12 ሆስፒታል 👉 ወረ ኢሉ ሆስፒታን፤
• ምኒሊክ ሆስፒታል 👉 መሃል ሜዳ ሆስፒታልን፤
• ጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል 👉 ከሚሴ ሆስፒታልን፤
• ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል 👉 ሀይቅ ሆስፒታልን፤
• ራስ ደስታ ሆስፒታል 👉 ደብረ ሲና ሆስፒታልን፤
• አለርት ሆስፒታል 👉 ኮምቦልቻ ሆስፒታልን፤
• ዘውዲቱ ሆስፒታል 👉 ደጎሎ ሆስፒታልን፤
• ጋንዲ ሆስፒታል 👉 ሞላሌ ሆስፒታልን፤
• አማኑኤል ሆስፒታል የአእምሮ ጤናና የስነልቦና ማህበራዊ አገልግሎት ድጋፍ 👉 ለሁሉም ሆስፒታሎች ድጋፍ ለመስጠት ትስስር በመፍጠር ወደ ስራ ገብተዋል።

ጤና ሚኒስቴር የአዲስ አበባ እና ፌዴራል ሆስፒታሎች እያደረጉ ስላሉት ርብርብ ምስጋና አቅርቧል።

ሆስፒታሎቹ በአፋጣኝ ስራ ለማስጀመር ከክልሉ እና ከጤና ሚንስቴር ጋር እየሰሩ ቢሆንም ሙሉ ለሙሉ ወደነበሩበት ለመመለስ አሁንም ከፍተኛ መዋለ ነዋይና ድጋፍ ስለሚያስፈልግ ሁሉም የሚመለከተው አካል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
#MoH

አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የጤና ሚኒስቴር አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ማስገባት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ጋር ተፈራረመ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ፕሮክጀቱ በብዙ ልፋት ተመርቀው ስራ ላይ ያልተሰማሩ ሃኪሞችን ወደ ስራ የሚያሰማራ በመሆኑ በጤናው ዘርፍ ትልቅ እምርታ ነው ብለዋል፡፡

ከተያዘው አመት ጀምሮ የሚተገበረው ይህ ፕሮጀክት የሶስት ዓመት ቆይታ እንደሚኖረው ገልፀዋል።

በመጀመሪያው ዓመት 2 ሺ 898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማሰማራት መታቀዱን ተናግረዋል።

ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልገው በጀትም የመጀመሪያው ዓመት ከፌዴራል መንግሥት እና ከአጋር ድርጅቶች በተገኘ ገንዘብ የሚሸፈን ሲሆን፥ ሁለተኛው እና ሶስተኛው ዓመት ከፌዴራል፣ ከክልልና ከከተማ አስተዳደሮች እና ከአጋር የልማት ድርጅቶች ድጋፍ በተገኘ ገንዘብ የሚተገበር ይሆናል።

ከአራተኛው ዓመት በኋላ ሙሉ በሙሉ በክልሎች አቅም እንደሚተገበርም ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የፈተና ውጤታችሁን ከነገ ጀምሮ መመልከት ትችላላችሁ። በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ከነገ ጀምሮ መመልከት ይቻላል። ከታህሳስ 21-27/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ የህክምና /Medicine/ ተመዛኞች ከየካቲት 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥር…
#MoH

በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ትላንት የካቲት 1 ይፋ ሆኗል።

ተመዛኞች ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ በ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እንዲሁም የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን እየተመለከቱ ነው።

በሌሎችም የሙያ ዘርፎች ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ውጤት በቅርብ ቀን ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ መረጃ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ የ2014 የሕክምና ሳይንስ /Medicine/ ተመራቂዎች #በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል።

ውድ ቤተሰቦቻችን የተለያዩ የ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መልዕክቶች በ @tikvahuniversity በኩል ማግኘት ትችላላችሁ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoH በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ትላንት የካቲት 1 ይፋ ሆኗል። ተመዛኞች ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ በ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እንዲሁም የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን እየተመለከቱ ነው። በሌሎችም የሙያ ዘርፎች ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ውጤት በቅርብ ቀን ይፋ ይደረጋል ተብሎ…
#MoH

ከዛሬ የካቲት 4 ጀምሮ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ውጤታቸው ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።

ከታህሳስ 21 - 27/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ከዛሬ የካቲት 04/2014 ዓ/ም ዓ.ም ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ውጤት የመመልከቻ አድራሻ hple.moh.gov.et ላይ ሲሆን ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤት መመልከት ይቻላል።

በውጤት ላይ ቅሬታ ያላቸው ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል hpcald@moh.gov.et ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማሩበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄያቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።

@tikvahethiopia
#MoH

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ፥ በሚኒስቴሩ ስፖንሰርነት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና የሕክምና ኮሌጆች የስፔሻሊቲ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች በያሉበት ተቋም የትምህርት ውል የሚገቡ መሆኑን ገለፀ።

የጤና ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት ተማሪዎቹን የትምህርት ውል እያስገባ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ የትምህርት ውል ማዋዋሉ በመደበኛ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና ከመፍጠሩ በተጨማሪ በተማሪዎች ላይም ከፍተኛ እንግልት እየፈጠረ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

በመሆኑም ተማሪዎቹ በያሉበት ተቋም ውል የሚገቡ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳው ወደፊት ይፋ ይደረጋል ብሏል።

@tikvahuniversity
#MoH

#ጨረታው_ተሰርዟል !

30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የወባ አጎበር ግዢ ጨረታ ተሰረዘ።

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት በኬሚካል የተነከረ የወባ መከላከያ አጎበር ግዢ በኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩል ግዢ እንዲፈጸም ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

በዚህም መሰረት ፤ ዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ወጥቶ ተጫራቾች ቀርበው አሸናፊውን ቢለይም በጨረታው ሂደት ላይ ቅሬታ መቅረቡን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ማጣራት በማድረግ ጨረታውን እንዲሰረዝ ማድረጉን አሳውቋል።

የጤና ሚኒስቴር በሌሎች ተቋማት የማጣራት ስራ መሰራቱን እንዲሁም ደግሞ በራሱ ባደረገው የማጣራት ስራ በጨረታ ሂደቱ ላክ የተፈጸመ ህገ-ወጥ ድርጊት እንዳላገኘ ገልጿል።

ነገር ግን " የብቃት ማረጋገጫ " እና " ምዝገባ " ጋር በተያያዘ በግብርና ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በህግ የተሰጠ ነገር ግን የስልጣን መደራረብ የነበረ መሆኑን እና የጨረታ መገምገሚያ መስፈርት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ቀርቦ ባለበት ሁኔታ ሂደቱን ከማስቀጠል የፋይናንስ ድጋፍ በሚያደርገው ድርጅት አማካኝነት ግዢው እንዲፈጸም ማድረግ ለሚኒስቴሩ የተሻለ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን በመገንዘብ ጨረታው እንዲሰረዝ ተደርጓል፡፡

(ተጨማሪ ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ProfessorSenaitFisseha ዛሬ የጤና ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ጋር ተፈራርሟል። ፕሮጀክቱ ዘንድሮ ጀምሮ ለ3 ዓመት ይቆያል። በመጀመሪያ አመት 2,898 ሃኪሞች ወደስራ ለማስገባት ታቅዷል። ለዚሁ ለመጀመሪያው ዓመት ስራ የሚያስፈልገው ገንዘብ ከፌዴራል እና ከልማት አጋር…
#MoH

➤ በአዲስ አበባ ለ161 ጠቅላላይ ሀኪሞች ቅጥር ወጥቶ ለመቀጠረ ያመለከቱት 2,300 ናቸው።

0⃣ በሶማሌ እና አፋር ክልል ለጠቅላላ ሀኪሞች የስራ ቅጥር ቢወጣም #ምንም አመልካች ጠቅላላ ሀኪም ለማግኘት አልተቻለም።

ጤና ሚኒስቴር እና ገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር 2,898 አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በሃገር አቀፍ ደረጃ በመቅጠር ወደ ስራ ለማሰማራት ከሁሉም ክልል ጤና ቢሮዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በተደረገ ስምምነት ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አንድ ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።

ይህ እኩል በእኩል መዋጮ ፕሮጀክት የሶስት ዓመት ፕሮጀክት ሲሆን በመጀመሪያዉ የፕሮጀክት ዓመት ወደ ስራ ለማሰማራት ከታቀደው 2,898 ጠቅላላ ሐኪሞች እና በተጨማሪ ከፕሮጀክቱ በጀት ዉጪ በክልሎች ተጨማሪ በጀት ➙ 961 ሃኪሞች በድምሩ ➙ 3,701 አዳዲስ ምሩቃን ጠቅላላ ሀኪሞች ለመቅጠር ከወራት በፊት በሁሉም የከተማ አስተዳደር እና የክልል ጤና ቢሮዎች የቅጥር ማስታወቂያ ወጥቶ ነበር።

የቅጥር ማስታወቂያ ቢወጣም አመልካች ጠቅላላ ሀኪሞች በሁሉም የቅጥር ማስታወቂያ በወጣባቸው ቦታዎች ላይ #በወጥነት እንዳላመለከቱ በተደረገ ክትትል ታውቋል።

ለአብነት ያህል ፤ አዲስ አበባ ላይ ለ161 የቅጥር መደብ 2,300 ጠቅላላ ሀኪሞች ናቸው ለመቀጠር ያመለከቱት።

ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ በአንዳንድ ክልሎች ለቅጥር ማስታወቂያ ከወጣባቸዉ መደቦች በጣም ባነሰ ቁጥር ያመለከቱ ሲሆን በአንዳንድ ክልሎች ደግሞ ምንም አመልካች አልተገኘም።

ምንም አመልካች ጠቅላላ ሀኪም ያልተገኘው ሶማሌ እና አፋር ክልሎች ላይ ነው።

እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 1,309 ጠቅላላ ሃኪሞች ብቻ የተቀጠሩ ሲሆን ይህም ከሚጠበቅው የቅጥር ብዛት አንፃር 35% ላይ ይገኛል።

ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ጠቅላላ ሃኪሞች በተለይም አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞች የቅጥር ማስታወቂያ በወጣባችው ክልሎች ፦
➡️ አማራ ክልል፣
➡️ አፋር ክልል፣
➡️ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
➡️ ጋምቤላ ክልል፣
➡️ ኦሮሚያ ክልል፣
➡️ ሲዳማ ክልል፣
➡️ ደቡብ ክልል፣
➡️ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እና ሶማሌ ክልል ለ2,392 ጠቅላላ ሃኪሞች ክፍት የሆነ የቅጥር ቦታ እንዳለ አውቀው እድሉን እንዲጠቀሙ ጤና ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#MoH

ሚሊኒየም አዳራሽ ለሚድሮክ ተመለሰ።

2 ዓመታት የኮቪድ -19 የህክምና እና የድንገተኛ ምላሽ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል የቆየውን አዲስ ፓርክ /የሚሊኒየም አዳራሽ/ ለባለቤቱ ተመለሰ።

ጤና ሚኒስቴር ሚሊኒየም አዳራሽን ከምስጋና ጋር ለባለቤቱ ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አስረክቧል።

የጤና ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዶከተር ሊያ ታደሰ ማዕከሉን ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባስረከቡበት ወቅት ምስጋና አቅርበዋል።

በተጨማሪ ፦ " ዛሬ የኮቪድ-19 የህክምና እና የድንገተኛ ምላሽ ማዕከሉን ዘግተን ወደነበረበት የምንመልሰው ኮቪድ ስለጠፋ ሳይሆን አገልግሎቱን በሌሎች የጤና ተቋማት ለማቅረብ የምንችልበት አቅም ስለፈጠርንና በመላ ሀገሪቱ የክትባት ሽፋንን በማድረስና የበሽታውን ጉዳት መቀነስ በመቻሉ ነው " ብለዋል፡፡

በቀጣይም ክትባቱን ያልወሰዱ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዲወስዱና ጥንቃቄያቸውን ሳይዘናጉ እንዲተገብሩ ማድረግ እንደሚገባ ማሳሰባቸውን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#MoH

የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና ምዝገባ ተጀመረ።

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በ2016 የትምህርት ዘመን በ21 የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች አመልካቾችን ተቀብሎ እንደሚያሰለጥን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና /ERMP/ መግቢያ ፈተና በመስጠት አወዳድሮ እንደሚያሰለጥን የገለፀ ሲሆን የህክምና ዶክትሬት ዲግሪ ያላቸውና የስፔሻሊቲ ስልጠና መውሰድ የሚፈልጉ ምዝገባ ማድረግ እንደሚችሉ ገልጿል።

ምዝገባው ከዛሬ ህዳር 06 ቀን 2016 ዓ /ም የሚጀምር ሲሆን ህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያበቃ አሳውቋል።

አመልካቾች የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ድረ-ገፅ www.moh.gov.et/ermp ላይ በመግባትና ለመሰልጠን በሚፈልጉት የስፔሻሊቲ ትምህርት ላይ በመመዝገብ መወዳደር እንደሚችሉ ተገልጿል።

ተመዝጋቢዎች ምዝገባውን ከመጀመራቸው በፊት ዝርዝር መረጃዎችንና መመሪያዎችን በዚህ ይመልከቱ ተብሏል👇
https://www.moh.gov.et/site/initiatives-4-col/ermp

@tikvahethiopia