TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋምቤላ ክልል ፡ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ከሕግ አግባብ ውጭ የተፈጸሙ የኃይል እርምጃዎች ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በጋምቤላ ከተማ፣ ጋምቤላ ክልል ከጠዋት እስከ ምሽት የቀጠለ ግጭት እና የፀጥታ እና የደኅንነት ችግርን ተከትሎ ለአንድ ቀን የከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶች፣ የንግድ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎችም አገልግሎቶች ተቋርጠው መዋላቸው ይታወሳል። ጥቃቱ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (በተለምዶ ኦነግ…
#Gambella

በጋምቤላ በዚህ ሳምንት ከተፈፀመው ጥቃት ጋር በተያያዘ ንፁሃን ዜጎች ላይ ከማዋከብ አንስቶ እስከ ግድያ የደረሰ ከዚህም በተጨማሪ የዝርፊያ ድርጊት መፈፀሙ መጠቆሙ ይታወሳል።

ክልሉ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ንፁሃን ሰለባ እንዳይሆኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረገ መሆኑን መግለፁ አይዘነጋም።

በከተማው አንድ ወጣት እጁን ወደ ኃላ ታስሮ የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ እና ባለሰቡ አካላት በጥይት ሲደብደብ የሚያሳይ ቪድዮ መሰራጨቱ በርካቶችን አስዝኖም አቆጥቶም ነበር ፤ ይህን ተከትሎ ክልሉ በሰጠው መግለጫ ይህንን ጉዳይ በግልፅ አፍረጥርጦ ባይናገርም ከህግ ውጪ የሆነ ድርጊት የፈፀሙና የስነ- ምግባር ጉድለት ያለባቸው የፀጥታ አካላት እንዳሉ አረጋግጦ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ መጀመሩን አስታውቆ ነበር።

ትላንት ሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት በወጣው ዘገባ ደግሞ ክልሉ አንድ ወጣት በጥይት የመደብደቡን ክስተት አረጋግጦ ፤ ከሕግ ውጪ ግድያ በፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች ላይ ዕርምጃ ተወስዷል ብሏል።

የጋምቤላ ክልል ኮሙዩኒኬሸን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡጉት አዲንግ " የኦነግ ሸኔና የጋምቤላ ነፃ አውጪ ቡድን አባላት ለይቶ ሕጋዊ ዕርምጃ የመውሰዱ ጥረት ፈታኝ ነበር " ያሉ ሲሆን " በዚህ የተነሳ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ወይም በእልህና በቁጣ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዕርምጃ የወሰዱ የፀጥታ አስከባሪዎች ነበሩ " ብለዋል።

#አንድ የልዩ ኃይልና #አንድ የመደበኛ ፖሊስን ጨምሮ ሁለት የፀጥታ አስከባሪዎች በሕገወጥ ግድያ ተጠርጥረው ተይዘዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

ጥቃት የከፈቱት ታጣቂዎች ሲቭልም የለበሱ ስለነበሩ እንዲሁም አንዳንዶቹ የትጥቅ ልብሳቸው ቀይረው ከህብረተሰቡ ጋር መቀላቀላቸው ሁኔታዎች ፈታኝ አድርጎት እንደነበርም ለጋዜጣው ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#China

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?

#ኢትዮጵያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።

አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።

#ሱዳን

ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።

ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።

#ኤርትራ

ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።

የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።

ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።

#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ለግል_መገልገያ_እንዲውሉ_ወደ_አገር_የሚገቡ_ወይም_ከአገር_የሚወጡ_ዕቃዎችን_ለመወሰን_የወጣ_መመሪያ_ቁጥር.PDF
ለግል መገልገያ ከቀረጥ እና ታክስ ነፃ ሆነው የሚገቡ ዕቃዎች የትኞቹ ናቸው ?

- ሲጋራ | መለኪያ ➤ ግራም |  የሚፈቀደው መጠን ➤ 200

- ሲጋር | መለኪያ ➤ በቁጥር |  የሚፈቀደው መጠን ➤ 20

- ብትን ትንባሆ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 250

- የአልኮል መጠጥ | መለኪያ ➤ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2

- ለስላሳ ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500

- ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500

- #ሞባይል | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2 (#ሁለት)

- #ላፕቶፕ | መለኪያ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን 1 (#አንድ)

- #የፎቶግራፍ_ካሜራ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- #ዊልቸር | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- #የእጅ_ሰዓት | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- የፂም ወይም የፀጉር መላጫ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- የፀጉር ማድረቂያ | መለኪያ ➤ በቁጥር |  የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- የፀጉር መተኮሻ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1

- መንገደኛው የሚጠቀምባቸው መድሃኒቶች እና የህክምና በቁጥር መገልገያዎች | መለኪያ ➤በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ሰው በሚያስፈልግ መመጠን

- በጉዞ ወቅት ጥቅም ላይ የሚውሉ እና ለቤተሰብ የሚያገለግሉ ፣ ልብሦች፣ ጫማዎች፣ እና የፅዳት እቃዎች | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ቤተሰብ ከሚያስፈልገው ያልበለጠ

የተሻሻለው የግል መገልገያ እቃዎች - የጉምሩክ መመሪያ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/73728

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ኢትዮጵያ ከፍላዋለች ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ አክብሮታል " - ድምፃዊት ትዕግስት አፈወርቅ

በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ እህት የሆነችው ድምፃዊት ትዕግስት አፈወርቅ አሁን ላይ በስደት #በካናዳ_ሀገር የምትገኝ ሲሆን የወንድሟን ህልፈት በሰማችበት ወቅት እራሷን ስታ ሆስፒታል እንደነበረች ተናግራለች።

ድምፃዊት ትዕግስት ፤ የወንድሟን ህልፈት ተከትሎ የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ላሳየው ልዩ ክብር ምስጋናዋን አቅርባለች።

ወንድሟን እስላም ፣ ክርስቲያኑ ፤ ኦሮሞው ፣ ትግራዩ ፣ አማራው አንድም ሳይለያይ አልቆሶ በክብር መቀበሩን የገለፀችው ትዕግስት ባየችው ነገር እንደተፅናናች ነገር ግን በኢትዮጵያ ውስጥ እየጠፋ ያለው የሰው ህይወት ይቆም ዘንድና ሁሉም ወደ ፍቅር እንዲመለስ እያለቀሰች ተማፅናለች።

ድምፃዊት ትዕግስት አፈወርቅ ፦

" ... ወንድሜን ኢትዮጵያ ከፍላዋለች። እግዚአብሔር ይመስገን የኢትዮጵያ ህዝብ አክብሮታል ፤ የኢትዮጵያ መንግስት አክብሮታል።

እንደ ንጉስ በክብር ተቀብሯል።

ፌንት አድርጌ ሆስፒታል ነበርኩኝ ፤ ወንድሜ ለኔ ልጄ ነው ፤ የስደት ጓዴ ነው፤ ሁሉ ነገሬ ነው። የጀግና ሞት ነው የሞተው፤ እንደ ንጉስ ነው የተቀበረው።

የማስተላልፈው መልዕክት ፤ ወንድሜ እንዲሁ እንደ ንጉስ እንደተቀበረ  ፤ #ኢትዮጵያን እንዳለ እንደዘፈነ ፤ ኢትዮጵያን እንደወደደ የክብር ሞት ነው የሞተው የኢትዮጵያ ህዝብም ብድሩን መልሶለታል።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ፤ ኢትዮጵያን ሰላም ያድርጋት።

ነገር ግን አንድ የሚያመኝ ነገር ወንድሜ እንዲህ እንደ ንጉስ ተከብሮ ተቀብሮ እንዲህ አንጀቴ ፣ ልቤ የተቆረጠ ፤ የሚያልቀው ህዝብ ፣ ምንም በማያውቀው ፣ ደጉ ባለሀገሩ ፣ ምስኪኑ የሚጨፈጨፈውስ ... ስለነሱ ነው መልዕክቴ።

የኢትዮጵያ ህዝብ እንደድሯችን #አንድ ልንሆን ይገባል፤ ሞት ሊቆም ይገባል። እኔ ወንድሜ በክብር ተቀብሮ እንደዚህ ያመመኝ ተዋግቶ በማያውቀው ተጋድሎ የሚሞተው ህዝብ ፤ ለእሱ ህዝብ ሞት ሊቆም ይገባል ነው መልዕክቴ።

ወንድሜማ እንደ ንጉስ ነው የተቀበረው ግን እንደዛም ሆኖ አንጀቴ ተቆርጧል። ማዲንጎ ኢትዮጵያን ነው ያሳየው እስላም፣ ክርስቲያኑ ፤ ኦሮሞው ፣ ትግራዩ ፣ አማራው ሁሉ አልቅሶ ነው የቀበረው። የኢትዮጵያ ህዝብ ደግ ህዝብ ነው።

እባካችሁ ወገኖቼ ፣ ወንድሜ እንዲህ በክብር ተቀብሮ እንኳን አዝኛለሁ አንጀቴ ተቆርጧል፤ እያየች ልጇ የሚገደልባት እናት አባት ፣ እህት ወንድም የሚያልቅው እባካችሁ ... እባካችሁ ሞት ይቁም ኢትዮጵያ ላይ ፤ እግዚአብሔርን አምላክን ፍሩ ፤ ሁላችንም እንፍራ ወደ ፍቅር እንምጣ።

ማዲንጎ ይጠበቃል ዱብእዳ ነው የሆነብኝ፤ ቀኝ እጄ ነው የተቆረጠው ... በሰው ሀገር ፌንት ነው ያደረኩት ግን የኢትዮጵያ ህዝብ አፅናናኝ ፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደዛ ሲሆንለት ሳይ ፣ ህዝቡ እንደዛ ሲወጣ አንድ አደረጋት ፣ #አንድ_ናት_ኢትዮጵያ እያለ ዘፍኖ ቀብሩ ላይ እስላም ፤ ክርስቲያን ሳይል ሁሉም አንድ ሆኖ ኦሮሞው ፣ ትግራዩ አንድ ሆኖ ነው አልቅሶ የቀበረው እናም ይሄ ህዝብ ፍቅር ነው የሚያስፈልገው ፤ ለእሱ ስንል መታሰቢያነቱ ለወንድሜ ይሁን አንድ ያድርገን እባካችሁ ፤ #ሞት_ይብቃን !! "

(ድምፃዊት ትዕግስት አፈወርቅ ፤ በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ላይ ለሚሰራጨው " ታዲያስ አዲስ " ለተሰኘው የሬድዮ ዝግጅት ከሰጠችው ቃል የተወሰደ)

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በዝርፊያ ምክንያት ኃይል ተቋርጧል።

ከጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ወደ ጃዊ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች #በሌቦች በመፈታታቸው ኃይል መቋረጡ ተገልጿል።

ይህንን ያሳወቀው የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ነው።

ዝርፊያው የተፈፀመው አይማ ገብርኤል ቀበሌ ጌሾ ወንዝ አካባቢ ነው።

ሦስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በሌባ በመፈታታታቸው የወደቁ ሲሆን አንድ ተጨማሪ ምሰሶ በመሳሳብ ጉዳት ደርሶበት ወድቋል።

በዚህ የተነሳ ፦ ለበለስ ስኳር ፕሮጅክት፤ ለጃዊና አካባቢው የሚሰጠው የጃዊ ኤሌትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጧል።

የወደቁትን ምሰሶዎች ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና የጀመረ ሲሆን ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ #አንድ_ሳምንት ሊፈጅ ይችላል ተብሏል።

ህብረተሰቡ የደረሰ ጉዳት እስኪጠገን በትዕግስት እንዲጠብቅ ዘራፊዎችን ለፀጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰላም ስምምነቱን አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና አቶ ጌታቸው ረዳ ተፈራርመዋል። ከተፈራረሙ በኃላም እጅ ለእጅ ተጨባብጠዋል። በአጠቃላይ የተደረሱትን የስምምነት ነጥቦችን የያዘው እና በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል (አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና አቶ ጌታቸው ረዳ) የተፈረመበት ወረቀት እንደደረሰን የምንልክላችሁ ይሆናል። @tikvahethiopia
#Update

ዛሬ በፕሪቶሪያ ፤ በኢትጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነትን በተመለከተ የወጣው የጋራ መግለጫ 12 ነጥብ የያዘ ነው።

ከዚህም ስምምነት መካከል ፦

- የህወሓት ቡድን #ትጥቅ_እንዲፈታ ከስምምነት ተደርሷል።

- የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ለማረጋገጥ እና የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥቱን ለማስከበር የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ተስማምተዋል።

- ኢትዮጵያ #አንድ ብሔራዊ መከላከያ ኃይል ብቻ አላት በሚለው ስምምነት ተፈርሟል።

- በመሬት ላይ ያለውን የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የህወሓት ተዋጊዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ተዋጊዎችን ከሠራዊቱ እንዲወጡ ለማድረግ እና መልሶ ወደ ማኅበረሰቡ ለመቀላቀል ስምምንት ላይ ተደርሷል።

- #የጥይት_ድምጽ_በዘላቂነት_እንዳይሰማ  በመስማማት፣ ጦርነቱ እንዲያበቃ የሚያስችል ዘላቂ የግጭት ማስወገድ ስምምነት ተፈርሟል።

-  በትግራይ ክልል ህገ መንግስታዊ ስርዓትን ወደነበረበት ለመመለስ እና የሽግግር እርምጃዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ስምምነት ተፈርሟል።

- የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ለማቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል።

- በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ስምምነት ተፈፅሟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ትግራይ ክልልም የክልሉን ግዛት እና ህዝቡን ለመጠበቅ በቂ የፖሊስ ኃይል፣ በቂ ልዩ ኃይል ፣ በቂ ሚሊሻ ይኖረዋል " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ቅዳሜ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የሰላም ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት " ህወሓት "ን ትጥቅ ስለማስፈታት እና በትግራይ ክልል ውስጥ ምርጫ ተከናውኖ የክልል መንግስት…
በሰላም ስምምነቱ መሰረት ፦

👉 በኢትዮጵያ ውስጥ #አንድ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ብቻ ይኖራል።

👉 በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መሰረት የህወሓት ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ መበተን እና ወደ ማኅበረሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የሚያስችል ዕቅድ ተነድፎ ተግባራዊ የሚሆንበትን ዝርዝር ይዘጋጃል።

👉 ከስምምነቱ መፈረም በኃላ የመንግስት እና ህወሓት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ይነጋገራሉ (የጦር አመራሮች የስልክ ንግግር ማድረጋቸው መነገሩ ይታወቃል) ።

👉 ስምምነቱ በተፈረመ በአምስት ቀናት ውስጥ በክልሉ ካለው ተጨባጭ ፀጥታ ሁኔታ በመነሳት ስብሰባ በማዘጋጀት የጦር አመራሮች የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት ላይ ይነጋገራሉ ፤ ስለሂደቱም ዝርዝር ያወጣሉ። (ይህ ከሰኞ ቀን 28/2/2015 ጀምሮ በኬንያ፣ ናይሮቢ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከህወሓት ጄነራል ታደሰ ወረደ በተገኙበት ተጀምሯል)

👉 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች #ከስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ባሉት #አስር_ቀናት ውስጥ የከባድ መሳርያ ትጥቅ የመፍታቱ ሂደት #ይጠናቀቃል። የተቀመጠው አስር ቀናት ጊዜ ገደብ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በሚሰጡት ሀሳብ እና በሁለቱ ወገኖች አጽዳቂነት ሊራዘም ይችላል።

👉 ከስምምነቱ በኋላ ባሉ 30 ቀናት ቀላል የጦር መሳርያዎችን ጨምሮ የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል።

👉 የህወሓት ታጣቂዎችን የማሰናበት እና መልሶ ወደ ማኅበረሰቡ የመቀላቀል ሥራ ሂደት የክልሉን ሕግ እና ፍላጎት መሠረት ያደርጋል።

@tikvahethiopia
#AxumUniversity

አክሱም ዩኒቨርስቲ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ የደረሰበት ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት ማስታወቁን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

ላለፉት 19 ወራት ትምህርት መስጠት አቁሞ የቆየው ዩኒቨርስቲው፤  ሊያከናውነው ላቀደው ዳግም ግንባታ የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የሰጡት ቃል ፦

- ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ሳቢያ በደረሰበት #ውድመት እና #ዘረፋ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉት ቁሳቁሶች እና መሳሪያዎች አጥቷል።

- ሙሉ ለሙሉ የተዘረፉ እና ከወደሙ የዩኒቨርስቲው ንብረቶች ውስጥ ኮምፒውተሮች፣ የላብራቶሪ መሳሪያዎች፣ ሰርቨሮች እና የቢሮ በሮች ይገኙበታል።

- ዩኒቨርስቲው ከጦርነቱ በፊት የነበሩት 60 ገደማ ተሽከርካሪዎች ተዘርፈው እና ተቃጥለው አሁን በስራ ላይ የሚገኘው #አንድ_መኪና ብቻ ነው።

- በጥር ወር ላይ በተደረገ ዳሰሳ የደረሰው ውድመት 15 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።

- ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶች በተወሰነ መልኩ በመተካት ወደ ስራ ለመግባት ታቅዷል።

- ለሚያከናውነው ዳግም ግንባታ እና ጥገና ስራ የገንዘብ እና የማቴሪያል ድጋፍ እንዲደረግልን  ጠይቀናል። የድጋፍ ጥሪው ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር በቀል አጋር ድርጅቶች፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ነው።

- ዩኒቨርስቲው የሚያገኘውን ድጋፍ በፌደራል መንግስት ከሚመደበለት በጀት ጋር በማጣመር በአጭር ጊዜ ውስጥ የመማር ማስተማር አገልግሎቱን ለመስጠት ታቅዷል። 

- ቁሳቁሶችን በተወሰነ መልክ ቅድሚያ እየሰጠን ካስገባን፤ የግዢ ሂደቱ ፈጣን ከሆነ፤ ተማሪዎችን #በሶስት_ወር ውስጥ ማስገባት እንችላለን። በትግራይ ክልል የሚኖሩ እና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ያቋረጡ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን ትምህርት ማስጨረስ ላይ ትኩረት ይደረጋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከፌደራል መንግስት በጀት ባይለቀቅለትም፤ በስሩ ለሚገኘው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 43 መምህራንን ለመቅጠር ከ2 ሳምንት በፊት ማስታወቂያ አውጥቷል።

የቅጥር ሂደቱ የሚፈጸመው በትምህርት ሚኒስቴር ተፈቅዶ፣ በጀት ሲለቀቅ መሆኑ ተገልጿል።

ከፌደራል መንግስት የሚለቀቀው በጀት፤ ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች ደመወዝ ለመክፈል እና ትምህርት ለማስጀመር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

#አራት_ሺህ ገደማ የሚሆኑት የዩኒቨርስቲው መምህራን እና ሰራተኞች ከሐምሌ 2013  ዓ.ም. ወር ጀምሮ #ደመወዝ_አለማግኘታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

Credit : www.ethiopianInsider.com

@tikvahethiopia
የካንሰር ህክምና . . . #በኢትዮጵያ

#ጥቁር_አንበሳ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል።

የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ኤዶም ሰይፉ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡

ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል።

በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነው።

ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ #አንድ ብቻ መሆኑን ነው።

በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000 ታካሚዎች ሲኖሩ፣ በማዕከሉ በቀን በአማካይ ከ300 በላይ ታካሚዎች ይስተናገዳሉ።

ከእነዚህ የካንሰር ታካሚዎች መካከል 70 በመቶ የጨረር ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፣ ኬሞ ቴራፒ የሚያስፈልጋቸው የታካሚዎች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም ።

በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የ2014 ዓ.ም. እና በ2015 ዓ.ም. ሕክምና ለማግኘት የተመዘገቡ ደግሞ ከ10,000 በላይ ናቸው። "

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ_ስፔሻላይዝድ_ሆስፒታል

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክሊኒካል ኢንኮሎጂስት ዶ/ር አማረ የሺጥላ ምን አሉ ?

"  በሆስፒታሉ የሚሰጠው የካንሰር ሕክምና ኬሞ ቴራፒና ቀዶ ጥገና ነው።

የጨረር ሕክምና ለመጀመር የማሽን ተከላ ላይ እንገኛለን። 60 በመቶ የሚሆነው የካንሰር ታካሚ እስኪጠናቀቅ እየተጠባበቁ ነው።

በሆስፒታሉ ካንሰር ሕሙማን ሕክምና አንዱ የሆነው ኬሞ ቴራፒ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ በዛ ከተባለ ከሳምንት አይበልጥም።

ይሁን እንጂ ለካንሰር ሕሙማን የሚሰጠው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመጠባበቅ ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት ያስፈልጋል። "

#በሐሮሚያ_ዩኒቨርሲቲ_ሕይወት_ፋና_ሆስፒታል

በሐሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ሕይወት ፋና ሆስፒታል በካንሰር ሕክምና ረዳት ፕሮፌሰር ሚካኤል ሻውል (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ሕክምና ለካንሰር ሕሙማን እየተሰጠ ነው።

የጨረር ሕክምና ከተጀመረ ስድስት ወራት አስቆጥሯል ፤ የታካሚዎች መጠነ መጠበቅ ከሦስት ወራት አይበልጥም።

በሆስፒታሉ በዓመት እስከ 6000 የካንሰር ታካሚዎች ሕክምና ያገኛሉ። በተለይ ደግሞ ጨረር ሕክምና ከተጀመረ በኋላ የታካሚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ በምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ጊዜያት ብቸኛው የካንሰር ሕክምና መስጫ በመሆኑ ከሶማሌላንድና ከሌሎች አገሮች እየመጡ አገልግሎት የሚያገኙ ነበሩ። "

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#State_of_Emergency የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ፤ በ " መጀመሪያ ምዕራፍ " ዕቅድ በትልልቆቹ የአማራ ክልል ከተሞች ፦ - ባሕር ዳር፣ - ደብረ ማርቆስ፣ - ደብረ ብርሃን፣ - ላሊበላ፣ - ጎንደር - ሸዋ ሮቢት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ " የሕግ የበላይነት እንዲከበር አስደርጌያለሁ " ብሏል። በእነዚህ ከተሞች " በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድንን…
#State_of_Emergency

ሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ።

በባሕር ዳር ፣ ጎንደር እና ደብረ ብርሃን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች የሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ትዕዛዝና ክልከላ አውጥቷል።

በዚህም ፤ ባሕር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ደብረ ብርሃን ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ እስከ ነሐሴ 17/2015 የሚቆይ የሠዓት እላፊ ገደብ ጥሏል።

- የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ከሚሰጡ ተሽከርካሪዎች፣
- የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ሰጪ ባለሞያዎች
- የፀጥታ አስከባሪ ተቋማት ባልደረቦች ውጪ ለማንኛውም ሰው እና ተሽከርካሪ ከምሽቱ #አንድ_ሰዐት_በኋላ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

የባጃጅ እና የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 17 2015 ድረስ ፈጽሞ መከልከሉ ተገልጿል።

ከባጃጆችና ከሞተር ሳይክሎች በስተቀር ሌሎች የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ከነሐሴ 4 ጀምሮ ወደ ሥራ የመመለስ እና አገልግሎት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

ከዚህ ባለፈ ፤ በባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ የሕዝብ የአገልግሎት ሰጪ፣ የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የንግድ ተቋማት ከነሐሴ 4/2015 ጀምሮ ክፍት እንዲሆኑ ታዟል።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ከፈቃዴ ውጪ በአማራ ብሔራዊ ክልል ከተሞች የአደባባይ ስብሰባ፣ ሰልፍና መሰል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ፈጽሞ የተከለከለ ነው ብሏል።

በማንኛውም መልኩ የህዝብ እንቅስቃሴን የሚያስተጓጉል እና የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሰናክል ድርጊትም በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስጠንቅቋል።

በተጨማሪ ፤ በክልሉ ለጸጥታ ሥራ ከሚንቀሳቀሱ የህግ አስከባሪ አካላት እና ከነዚህ አካላት ፈቃድ ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መዘዋወር ፈጽሞ ተከልክሏል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሽፋን ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ትእዛዝ ውጭ ወቅታዊ ሁኔታን ሰበብ በማድረግ ግለሰቦችን ከመደበኛው ህግ አግባብ ውጪ ማሰር እና ማቆየት፣ የንግድ ቤቶችን ማሸግ እና መሰል እርምጃዎችን መውሰድ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#April6RWANDA "...እ.ኤ.አ ሚያዝያ 6/1994 በጊዜው የሩዋንዳ ፕሬዝዳንት የነበሩትን ጁቬናል ሃብያሪማናንና የቡሩንዲውን አቻቸውን ሲፕሬን ንታርያሚራን የያዘ አውሮፕላን ተመትቶ 2ቱን ፕሬዚዳንቶች ጨምሮ በአውሮፕላኑ ውስጥ የተሳፈሩት ሁሉም ሰዎች አለቁ፡፡ ፕሬዚዳንት ሃብያሪማና የሁቱ ጎሳ ተወላጅ መሆናቸው በወቅቱ ስልጣን ይዘው የነበሩት ሁቱዎች ለረጅም ዓመታት በሩዋንዳ የመንግሥትን ስልጣን…
#ሩዋንዳ

ዛሬ የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) 30ኛ ዓመት መታሰቢያ ነው።

በ1994 እ.አ.አ ሩዋንዳ ውስጥ በቱትሲ ጎሣ ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ዘመቻ በሰው ልጆች ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከደረሱት አሰቃቂ የዘር ጭፍጨፋዎች አንዱ ነው።

በ100 ቀናት ገደማ ውስጥ ብቻ ከ800,000 እስከ 1,000,000 የሚሆኑ ሰዎች እንዳለቁ ይገመታል።

ከተገደሉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ቱትሲዎች ናቸው፤ ሆኖም በጭፍጨፋው ለመካፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ የሁቱ ጎሣ አባላትም የግድያው ሰለባ ሆነዋል።

በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ተደፍረዋል።

የሩዋንዳ ጄኖሳይድ እንዴት ተፈፀመ ?

- በ10 ሚሊዮን የሚቆጠሩ የሩዋንዳ ዜጎች ለዘመናት እራሳቸውን እንደ #አንድ ነው ሲያዩ የኖሩት።

- በ1916 (እ.አ.አ) ቤንጂየም ሩዋንዳን በቅኝ ግዛት ትይዛታለች። በኃላም በቁጥር የሚበዙትን ሁቱዎች በቁጥር ከሚያንሱት ቱትሲዎች የሚለዩበትን አዲስ ሲስተም የመታወቂያ ወረቀት በመስጠት ዘረጋች። (የብሄር መታወቂያ አከፋፈለች)

- ቱትሲዎቹ በቤልጂየምዎቹ ፦
° በትምህርት ፣
° በስራ፣
° በስልጣን ከፍ ያለ ቦታ እንዲሰጣቸው ተደረገ። ሁቱዎቹ ግን ብዙ ቁጥር ኖሯቸው የትምህርት ፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ተነፈጋቸው።

- ቤንጂየሞቹ ቱትሲዎቹ ከብዙሃኑ ሁቱዎቹ የተሻሉ አድርገው እንዲሳሉ አደረጉ።

- በ1959 ሩዋንዳ ነጻነቷን ስታገኝ ሁቱዎች በማመፅ እና የመንግሥትን ስልጣን በመያዝ #ቱትሲዎችን ገደሉ ፣ ከሀገር እንዲሰደዱ አደረጉ። በዚህ ወቅት በመቶ ሺዎች ወደ ጎረቤት ሀገር ተሰደዋል።

- በ1990 በቱትሲ የሚመራው የRwanda Patriotic Front (RPF) ከኡጋንዳ በመሆን በሁቱ በሚመራው መንግሥት ላይ ጥቃት ከፈተ። ይህም የእርስ በእርስ ጦርነት መጀመሪያ ሆነ። በዚህ ወቅት ፈረንሳይ የሩዋንዳን መንግሥት ታስታጥቅ፣ ታሰለጥን ፣ ትደግፍ ነበር። ሩዋንዳም በፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አማካኝነት በፖል ካጋሚ የሚመራውን ኃይል ትደግፍ ነበር።

- በሩዋንዳ መንግሥትና በRPF ኃይል መካከል የነበረው ጦርነት በ1993 የሰላም ስምምነት እንዲቆም ተደረገ። የUN ኃይልም ስምምነቱ እንዲከበር ለማመቻቸት ዘንድ ወታደራዊ ኃይሉን ላከ።

- በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ በሁቱ እና በቱስቲዎች መካከል ያለው ውጥረት እጅግ በጣም እየከፋ ነበር የሄደው። የጥላቻ ፕሮፖጋንዳውን ከፍ ብሎ ነበር። በእርስ በእርስ ጦርነቱ ወቅት የሩዋንዳ መንግሥት RPFን እንደ ጠላት፣ እንደ ሀገር ካጅ፣ ባንዳ፣ እያደረገ ፕሮፖጋንዳ ሲሰራ ነበር።

-  ሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሁቱ ጎሳው ፕሬዜዳንት ጁቬናል ሃብያሪማና ተሳፍረውበት የነበረው አውሮፕላን ኪጋሊ በሚገኝ ኤፖርት አካባቢ ተመትቶ ወደቀ። ፕሬዜዳንቱም ህይወታቸው አለፈ። በወቅቱ የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ሳይፕሪን ንታያሚራ አብረዋቸው ነበሩ እሳቸውም ሞቱ።

- ፕሬዚዳንቱን የገደላቸው ማን እንደሆነ በግልጽ ባይታወቅም ሁቱዎቹ የቱትሲ አማፂ ቡድን ነው የፈፀመው ብለው በሚዲያ አስወሩ። ሁቱዎች እየወጡ ቱትሲዎችን እንዲገድሉ በሚዲያ ጥሪ አቀረቡ።

... በቃ #ግድያው ተጀመረ። ከ800 ሺህ እስከ 1,000,000 ቱትሲዎች እና ለዘብተኛ ሁቱዎች አለቁ። ከ100 ቀን በኃላ የRPF ኃይል ወደ ኪጋሊ ሲቃረብ ግድያው አቆመ ሁቱዎቹም መሸሽ ጀመሩ፣ በተለይ ሲገድሉ ሲያስተባብሩ የነበሩት ሀገር ጥለው ወጡ።

ሚዲያዎች ? የውጭ ሀገር ኃይሎች ? ተመድ በዚህ ውስጥ ምን ሚና ነበራቸው ? በቀጣይ  ፅሁፍ እንዳስሳለን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ለ2017 በጀት አመት 1 ትሪሊዮን የሚጠጋ በጀት ቀረበ።

ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

በዚህም ስብሰባው ላይ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ አንዱ ደግሞ የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ነው።

በዚህም ፦
➡️ ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣
➡️ ለካፒታል ወጪዎች ፣
➡️ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣
➡️ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ
➡️ ተጠባባቂ ወጪን ጨምሮ ወደ #አንድ_ትሪሊየን የሚጠጋ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2017 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

(ተጨማሪ መረጃ እና ሌሎች ውሳኔዎች ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#Ethiopia #ፍትሕ

በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ የተገደለችው የ7 ዓመቷ ህጻን ሔቨን ታሪክ የበርካቶችን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሆኗል።

ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዛሬ #አንድ_ዓመት በፊት በባህርዳር ከተማ እንደሆነ ዛሬም ድረስ መሪር ሀዘን ውስጥ የምትገኘው እናት " ኢዮሃ " በተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርባ ተናግራለች።

ህጻን ሔቨን የተደፈረችው ተከራይተው ይኖሩበት በነበረ ግቢ አከራይ ነው።

የተደፈረችበት መንገድም ወደ ሽንት ቤት በምትሔድበት ጊዜ ጠብቆ ወደ ቤት በማስገባት ነው። እጅግ በጣም አሰቃቂም ነበር።

ህጻን ሔቨንን የደፈረው ወንጀለኛ በምትደፈርበት ወቅት አንገቷን አንቆ ፤ አፏን አፍኖ ድርጊቱን የፈጸመ ሲሆን ወድቃ የሞተች ለማስመሰል ደሟን አንጠባጥቦ በር ላይ ጥሏት መሄዱን እናት ታስረዳለች።

እናት ልጇን ብቻ አይደለም ያጣችው ፤ ፍትህ ስትጠይቅ ይህንን ግፍ ሰምተው እንዳልሰማ የሆኑ ጎረቤት እና ቤተሰቦች ፤ በጥቅም ወንጀለኛውን ነጻ ለማስወጣት የሰሩ ፤ እናትን ጭምር ተባብረው ለማጥፋት ረጅም ርቀት የተጓዙ ፤ ማስፈራሪያ ደርሷቸው ቃላቸውን ከመስጠት የጠፉ ሁሉ ለእናት ፈተና ሆነውባታል።

ይህም ሆኖ ጥቂት የሚባሉ (የሴቶች እና ህጻናት ወንጀል መሪማሪ ፖሊሷ፤ የሴቶችና ህጻናት ቢሮ) አንዳንዶቹ ማስፈራሪያ ጭምር እየደረሳቸው አግዘዋት ከብዙ መከራ በኋላ ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ይፈረድበታል።

እናት ግን ዛሬም ትኩስ ሀዘን ላይ ነች።

ሥራ እየሰራች መኖር አልቻለችም።

ነገ ከእስር ሲለቀቅ እሷንም ጭምር ለመግደል እንደሚፈልግ ፤ ለዚህም ደግሞ ዳግም ሥራ ከጀመረችበት ቦታ ቤተሰቦቹ ተከታትለዋት ጥላ መውጣቷን እናት አስረድታለች።

ዛሬም እውነተኛ ፍትሕ አጥታ ትንከራተታለች።

ግፍ ላይ ግፍ !

በመሰረቱ በዚህች ምስኪን አንድ ፍሬ ፤ ክፉ ደግ በማታውቅ ህጻን ላይ አሰቃቂ የመድፈር እና ኃሏም ህይወቷን ያሳጣ የወንጀል ድርጊት የፈጸመ ሰው እንዴት 25 ዓመት ይፈረድበታል ? እውነት ይህ ማስተማሪያ ነው ? ወይስ ሌላ ነው ዓላማው ?

የሔቨን ታሪክ የብዙ ህጻናት ታሪክ ጭምር ነው።

ከዚህ በፊት ሴቶች፣ ህጻናት ጭምር ሲደፈሩ የሚተላለፉ የፍርድ ውሳኔዎች ህዝቡን እያስቆጣ መሆኑን አሳውቀን ነበር።

ዛሬም ፍትሕ ተጓድሏል። ፍትሕ ይስፈን።

ዛሬ አጋጣሚ ይህ ጉዳይ አደባባይ ወጣ እንጂ ስንቷ እናት ቤቷ ዘግያ እያለቀሰች ይሆን ? ስንት ሴቶች በግፍ ሰለባ ሆነው እያነቡ ይሆን ?

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia