TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UPDATE

የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበርና የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፎሳ በኢትዮጵያ በትግራይ ክልል የተከሰተውን ግጭት በተመለከተ ከጠ/ሚር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር እንዲወያዩ የተሰየሙት ልዑካን ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) መግባታቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።

ይህ ልዑክ የቀድሞውን የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት ዮአኪም ቺሳኖ ፣ የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ሰርሊፍ ጆንሰንና የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዝደንት የነበሩትን ጋሌማ ሞትላንቴ የያዘ ነው።

3ቱ የቀድሞ መሪዎች "ግጭቱ የሚያበቃበትን" መንገድ ለመወያየት ነው አዲስ አበባ የመጡት።

ልዑኩ ወደ አዲስ አበባ የገባው መንግስት የህግ ማስከበር እርምጃው ወደ #መጨረሻው ምዕራፍ ተሸጋግሯል ብሎ ባሳወቀበት ጊዜ ነው።

ዛሬ ጥዋት ጠ/ሚር ዶ/ር አብይ አህመድ በመቐለ የሚካሄደው የ3ኛው ምዕራፍ ኦፕሬሽን መጀመሩን አሳውቀዋል።

ጠ/ሚር ዶ/ር አብይ አህመድን ጨምሮ ሌሎችም የፌዴራል ባለስልጣናት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ሕግን ማስከበበር ስለሆነ ከህወሓት አመራሮች ጋር ምንም አይነት ድርድር ለማድረግ ፍላጎት እንደሌለ ከዚህ ቀደም መግለፃቸው ይታወቃል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከምን ደረሰ ? " ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ መንገድ ይጠርጋል " የተባለው የመግባቢያ ስምምነት ከሶማሌለንድ ጋር ከተፈረመ ትላንት 1 ወር አልፎታል። የመግባቢያ ስምምነቱ እኤአ ጥር 1 ነበር የተፈረመው። ይህ ስምምነት በተፈረመበት ወቅት በመንግሥት ባለስልጣናት በኩል በተሰጡ ገለፃዎች ፦ * በ1 ወር ውስጥ የስምምነቱ ዝርዝር ይፋ እንደሚደረግ፤…
" ... ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ ከእነሱ ጋር ቢዝነስ መስራት እንፈልጋለን " - ሰኢድ ሀሰን አቡዱለሂ

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች / #UAE / ንብረት የሆነው ' ዲፒ ወርልድ ኩባንያ ' የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለስልጣናት ማቀዳቸው ተሰምቷል።

ለዚህ የወደብ አጠቃቀምና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሌላንድ መካከል መፈረም አለበት።

ስምምነቱ ወደ መጨረሻውው ምዕራፍ መድረሱንና በሚቀጥሉት 60 ቀናት ተጠናቆ ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር አሳውቋል።

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሰኢድ ሀሰን አቡዱለሂ ፥ " ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ ከእነሱ ጋር ቢዝነስ መስራት እንፈልጋለን በአሁን ወቅት የወደብ አጠቃቀም ስምምነት ወይም Transit Agreement እያዘጋጀን ነው። አንዴ ስምምነቱን ከተፈራረምን በመጀመሪያው ዓመት ከኢትዮጵያ ጭነት 30% እናስተናግዳለን " ብለዋል።

ይህን በተመለከተ " ስምምነቱ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸው በአንድ ወይም ሁለት ቀሪ ጉዳዮች ላይ እየተወያየን ነው ምናልባት በመጪዎቹ 60 ቀናት ሊጠናቀቅ ይችላል ከ60 ቀናት በኃላ እንፈራረማለን " ሲሉ ተደምጠዋል።

ከወራት በፊት እ.አ.አ ጥር 1 ላይ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላድ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በተመሳሳይ ወደ ተግባር የሚገባበት የመጨረሻው ስምምነት በ2 ወራት ገደማ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሌላንድ ባለስልጣናት ገልጸዋል።

መግባቢያ ምምነቱ ከተፈረመ በኋላ ውይይቶች ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን የቴክኒክ ኮሚቴዎችም መታጨታቸውን ተናግረዋል።

ይህ የመግባቢያ ስምምነት ወደ #መጨረሻው ደርሶ ወደ ተግባር ከገባ ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ የባህር ዳርቻ የጦር ሰፈር በሊዝ ኪራይ የምታገኝ ሲሆን ሶማሌላንድ በበኩሏ ለረጅም አመታት ስትፈልገው የነበረውን እውቃና የማግኘት እድል እንደሚፈጥርላት ባለስልጣናቱ አመልክተዋል።

ለንግድ ስራ ሌላ ወደብ መገንባት ሳያስፈልግ የበርበራ ወደብን ኢትዮጵያ እንደምትጠቀምበት ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia