TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ!

TechTalk With Solomon⬇️

"ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ! በርካቶች በኢትዮጵያ እና በሌላም ቦታ ያሉ ሰዎች "እኛ አናደርግላችኋለን" በሚሉ አጭበርባሪዎች በኩል #የቢትኮይን ኢንቨስትመንት ውስጥ እየገቡ እንዳለ እየተነገረኝ ነው! አንድ ጠቃሚ ምክር ልስጣችሁ፤ ማንም ሰው ወደናንተ ቀርቦ ሃብታም አደርጋችኋለሁ እያለ ለፍታችሁ የሰራችሁትን ገንዘብ ለዚህ ጉዳይ ቢጠይቃችሁ ፍጹም እንዳታረጉት! ይህ በአሁን ሰዓት እየተበራከተ ያለ ወንጀል/#ማጭበርበር ነው።

"ሰዎች ብር ሲሰሩ እያየሁ ነው" ትሉ ይሆናል። ይህ አይነት ወንጀል #ከክሪፕቶከረንሲ በፊትም የነበረ ሲሆን፣ ነገሩ እንዲህ ነው -በኢንቨስትመንት ዓለም የሚታወት አንድ አደገኛ ወንጀል አለ "ፖንዚ ስኪም" ይባላል። ይህ ማለት ገንዘባችሁን በናንተ ስም ኢንቨስት አድርጌ #ትርፍ አመጣላችኋለሁ የሚለው አካል አብዛኛውን ገንዘብ ራሱ ከበላ በኋላ፣ ከአዲሲሶቹ ተጠቂዎች የሰበሰውን ለበፊቶቹ ተጠቂዎች በመስጠት በእርግጥ ትርፍ እያስገኘ እንዳለ ማስመሰል ነው። ከዚህ ወንጀል በጣም በጣም በጣም ተጠበቁ!

ክሪፕቶከረንሲ ላይ እጅግ በመጠኑ ኢንቨስት ማድረግ ከተፈለገ (አሁን ብዙም ባይመከርም) በትክክለኛ ሁኔታ እና በታወቁ አፖች (መተግበሪያዎች) በራሳችሁ ማድረግ ትችላላችሁ (ችግሩ በኢትዮጵያ የባንክ ካርድ አሰራር ማነስ እና እነዚህ አፖች ምናልባትም በኢትዮጵያ ላይሰሩ መቻላቸው ነው)"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የገቢዎች ሚኒስቴር‼️

የ14 ቢሊየን ብር የታክስ ስወራ እና ማጭበርበር የፈፀሙ 105 ግለሰቦች #በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስትሯ ወይዘሮ #አዳነች_አቤቤ በሰጡት መግለጫ የህዝብን ሀብት በመበዝበር እና የታክስ ማጭበርበር በመፈፀም የተለዩ 135 ድርጅቶች መለየታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በታክስ ስወራው ከተጠረጠሩት 105 ግለሰቦች መካከል 64 የሚሆኑት ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ነው ሚኒስትሯ የተናገሩት፡፡

ሚኒስትሯ በመግለጫቸው 9 ቢሊየን ብሩ 100 ቀናቱ የተለዩ መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን ቀሪው 4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በጥርና የካቲት ወር የተለየ እንደሆነ አንስተዋል፡፡ የታክስ ስወራና ማጭበርበር ላይ በዋነኝነት ተሳታፊ ሆነው የተገኙት አከፋፋዮች እና አስመጪዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ማለትም 30 በመቶዎቹ ብቻ ቸርቻሪ መሆናቸውን በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሯ በታክስ #ስወራና #ማጭበርበር የተለየውን 14 ቢሊየን ብር ድርጅቶቹ ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ባለፈ ህግ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተናገሩት ሚኒስትሯ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን አስታውቀዋል፡፡

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia