TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Adwa128

የሀገር መከላከያ ሠራዊት የዘንድሮው 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል በተለያዩ ስነስርዓቶች እንደሚከበር አሳውቋል።

በዓሉ በአ/አ ፒያሳ በሚገኘው የ " ዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም " እንደሚከበር ገልጿል።

የዓድዋ ጀግኖችን የሚዘክር የ34 ደቂቃ ዶክመንታሪ ፊልም፣ ቢል ቦርድ፣ በራሪ ወረቀቶች፣ ሎጎ፣ መሪ ቃል እና ሠራዊቱ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ሆኖ የሚወያይበት ፅሁፍ ተዘጋጅቷል ተብሏል።

በዕለቱ የካቲት 23 ቀን ወታደራዊ የሰልፍ ትርኢት እና ድሉን የሚያስታውሱ ልዩ ልዩ ትርኢቶች ፒያሳ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይቀርባል ተብሏል።

@tikvahethiopia