TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Amhara

የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን የገና በዓል እና የጥምቀት በዓል በሰላምና ያለምንም የፀጥታ ስጋት እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል።

የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልል የጸጥታ እና የደህንነት አካላት ጋር በጥምረት በመሆን በዓሉ በሰላም ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ እና የፀጥታ ኃይሉ ስነምግባርን ተላብሶ ተግባራትን እንዲከዉን ዝርዝር ዕቅድ ታቅዶ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና አባላት በቂ ኦረንቴሽን በመስጠት ዝግጅት ተደርጓል።

በተለይ ደግሞ በዓሉ በከፍተኛ ሁኔታ በሚከበርባቸው አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ እና ቋሚ ጥበቃ ተመድቧል። በዚህም ህዝቡ በዓሉን ያለምንም የፀጥታ ስጋት ሊያከብር ይገባል ተብሏል።

ህዝቡ ከፀጥታ ኀይሎች ጎን በመሆን በዓላቱ በሰላም እንዲከበር የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተገልጿል።

ነዋሪዎች በአማራ ክልል ማንኛውም አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥም በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ኀይል እንዲጠቁሙ መልዕክት ተለልፏል።

(የዞኖች ፣ የብሄረሰብ አስተዳደሮች እና ከተሞች የፖሊስ ስልክ ከላይ ተያይዟል - በምትኖሩበት አካባቢ ሁሌም የፀጥታ ኃይሎችን ስልክ ቁጥር መመዝገብ እንዳትዘነጉ)

እባክዎትን ስልክ ቁጥሮቹን #Share #ሼር ያድርጉ !

#AmharaPoliceCommission

@tikvahethiopia