TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፌስቡክ‼️

የማይናማር #ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ መዋሉን ሪፖርት ጠቆመ።

ፌስቡክ በማይናማር ከ18 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት። ፌስቡክ ለበርካቶች ዋነኛው ወይም ብቸኛው የመረጃና የዜና ምንጭ ነው።

የፌስቡክ አስተዳደሮች “በማይናማር እየገጠመን ያለውን ችግር ለመቅረፍ እየሠራን ነው። ሆኖም ብዙ ይቀረናል” ብለዋል።

ባለፈው ዓመት የሮሂንጋ ታጣቂዎች ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ የሃገሪቱ ጦር ራክሂን በምትባለው ግዛት ላይ
መጠነ ሰፊ ጥቃት ሰንዝሮ ነበር።

በሺዎች የሚቆጠሩ ህይወታቸውን ሲያጡ፤ ከ700 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሃገር ባንግላዲሽ ተሰደዋል። በሮሂንጋውያን ላይ የአስገድዶ መድፈር፣ የእርሻ መሬትን መቃጠልና መሰል በደሎች ሮሂንጋውያን በማይናማር (በርማ ተብላ ትጠራ በነበረው) ሃገር ውስጥ እንደ ስደተኛ ይቆጠራሉ። በመንግሥት እና በተቀረው ሕዝብ
ለበርካታ አስረት ዓመታት ተገልለዋል።

ቢዝነስ ፎር ሶሻል ሪስፖንሲቢሊቲ (Business for Social Responsibility -BSR) ያቀረበው ባለ 62 ገጽ ገለልተኛ ሪፖርት ”በማይናማር ግጭትና ጥላቻን ማባባስ ለሚፈልጉ ቡድኖች ፌስቡክ መጠቀሚያ ሆኗል” ይላል።

ሪፖርቱ፤ ፌስቡክ #የጥላቻ_ንግግርን በተመለከተ ያለውን ፖሊሲ እንደገና ሊከልሰው ይገባል ሲልም አክሏል።

ምንጭ፦ ቫይስ ኒውስ(በጌጡ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በጎንደር ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀስቅሷል"

ዛሬ ይህን መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲሰራጭ ተመልክተን ጎንደር የሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላትን ጠይቀናቸው "ነጭ ውሸት" ነው ወጣቱ ከመከላከያ ጋር አልተጋጨም፤ ህዝባዊ ተቃውሞ የሚያስብል አይደለም ብለውናል። ህዝቡም ከእንዲህ ያሉ #ግጭትን ከሚቀሰቅሱ እና ከሚያባብሱ #ሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲያርቅም መክረዋል።

•Ethiopian Dj ~ የፌስቡክ ገፅ
•የተከታዮቹ ብዛት:1,928,218

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቲክቶክ ወደ ፍርድ ቤት አመራ። ቲክቶክ የተሰኘው የቪድዮ ማጋሪያ የማህበራዊ ሚዲያ ለአሜሪካ ኩባንያ የማይሸጥ ከሆነ በመላ አሜሪካ ለመታገድ ተቃርቧል። እግዱ ተግባራዊ እንዳይደረግ ወይም ውድቅ እንዲሆን ቲክቶክ ወደ አሜሪካ ፍርድ ቤት አምርቷል፤ ሙግትም ከፍቷል። መተግበሪያው ለፍ/ቤት ባቀረበው የአቤቱታ መዝገብ " ከ9 ወር - 1 ዓመት ባለው ጊዜ ቲክቶክ ካልተሸጠ #ይታገድ " የሚለው ሕግ ኢ-ሕገመንግስታዊ…
'ቲክቶክ' ን ሙሉ በሙሉ / በከፊል ያገዱ ሀገራት የትኞቹ ናቸው ?

1ኛ. ህንድ

ቲክቶክን ያገደችው በ2020 ላይ ነው። በድንበር አካባቢ ከቻይና ጋር የተፈጠረው #ግጭትን ተከትሎ ነው ለደህንነት በሚል ቲክቶክን እና ሌሎች ከቻይና ጋር የተገናኙ መተገበሪያዎችን ያገደችው።

በወቅቱ በሀገሪቱ 200 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ነበሩ።

2. አፍጋኒስታን

ቲክቶክን በ2022 ያገደች ሲሆን ምክንያቷ ደግሞ ወጣቱ ትውልድ በተሳሳተ አቅጣጫ እንዳይሄድ ለመከላከል ነበር።

3.  አውስትራሊያ

በፌዴራል መንግሥት ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ ማሳሪያ ላይ እንዳይሰራ ተደርጓል። ከደህንነት ጋር በተያያዘ

4. ቤልጂየም

ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ ቲክቶክን በፌደራል የህዝብ አገልግሎት መሳሪያዎች ላይ እንዳይሰራ ጊዜያዊ እገዳ ጥላለች።

5. ካናዳ

ከደህንነት ጋር በተያያዘ የፌዴራል መንግሥት መሳሪያዎች ላይ ታግዷል።

6. ዴንማርክ

የሀገር መከላከያው ሚኒስቴር ማንኛውም ሰራተኛ በስራ ስልኩ ቲክቶክ እንዳይጠቀመ ያገደ ሲሆን ሁሉም ሰራተኛ ጭኖት የነበረውን መተግበሪያ እንዲያጠፋ አስደርጓል።

7. የአውሮፓ ህብረት

ሰራተኞች ሚጠቀሙበት መሳሪያ ላይ ታግዷል። የፓርላማው ህግ አውጭዎች እና ሰራተኞችም ከኤሌክትሮኒክ መሳሪያቸው ላይ እንዲያስወግዱ ተደርጓል።

8. ፈረንሳይ

ከደህንነት ጋር በተያያዘ ቲክቶክና ሌሎች እንደ X ፣ ኢንስታግራም ያሉ መተግበሪያዎችን የመንግስት ሰራተኞች ስልካቸው ላይ ለ 'መዝናኛ' በሚል እንዳይጠቀሙ ታግደዋል።

9. ላቲቪያ

ከደህንነት ጋር ተያይዞ በሁሉም የላቲቪያ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ኤሌክትሮኒክስ እንዳይሰራ ታግዷል።

10. ኔዘርላንድስ

ማዕከላዊ መንግሥት ቲክቶክ ጨምሮ ሌሎችንም መተግበሪያዎች ከደህንነት ጋር በተያያዘ ከሰራተኞች ስልክ ላይ እንዲታገዱ አድርጓል።

11. ኔፓል

ማህበራዊ መስተጋብር በመሸርሸር፣ ወጣቶችን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ በመውሰድ በሚል ሙሉ በሙሉ ነው ያገደችው።

12. ኒውዚለንድ

የፓርላማው ህግ አውጪዎችና ሰራተኞች በሙሉ ስልካቸው ላይ ቲክቶክ እንዳይኖር ታግደዋል፤ ይህ ከደህንነት ጋር በተያያዘ ነው።

13. ኖርዌይ

ከመላው የኖርዌይ ፓርላማ የስራ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ላይ እንዲታገድ ተደርጓል። የመንግስት ሰራተኞች ስልካቸው ላይ እንዳይጭኑ ታዟል።

14. ፓኪስታን

ከ2020 ጀምሮ ቢያንስ ለአራት ጊዜ በጊዜያዊነት አግዳለች ይህም ከስነ ምግባር ያፈነገጠ ይዘትን ያስተዋውቃል በሚል ነው።

15. ሶማሊያ

መንግሥት ቲክቶክ፣ ቴሌግራምና 1 የቁማር ድረገጽ እንዳይሰሩ እንዲያደርጉ አዟል። መተግበሪያዎቹ የጽንፈኝነት መፈንጫ ሆነዋል በሚል ነው።

16. ታይዋን

ከደህንነት ጋር ተያይዞ ከሁሉም መንግሥታዊ መሳሪያዎች ከስልክ ፣ ታብሌት ፣ ኮምፒዩተር ፣ እንዳይሰራ ተደርጓል።

17. ዩናይትድ ኪንግደም

የመንግስት ሚኒስትሮችና የመንግስት ሰራተኞች ከሚጠቀሙባቸው የሞባይል ስልኮች እንዳይሰራ ታግዷል። ፓርላማው ከኦፊሴላዊ መሳሪያዎችና ኔትዎትክ ላይ አግዷል። ይህ ከደህንነት ጥንቃቄ ጋር በተያያዘ ነው።

18. ኪርጊስታን

የልጆች አእምሯዊ፣ መንፈሳዊ እና ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም በሚል ቲክቶክን በሙሉ አግዳለች።

19. አሜሪካ

ከደህንነት ጋር በተያያዘ ከፌደራል ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች እንዲታገድ ተድርጓል። ከ50 ግዛቶች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መተግበሪያውን ከይፋዊ የመንግስት መሳሪያዎች ላይ አግደዋል።

አሁን ሙሉ በሙሉ ልታግድ ጫፍ ደርሳለች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፤ መረጃውን ያሰባሰበው ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ነው።

@tikvahethiopia