TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቁልቢ #ሀዋሳ #ሀምሌ19

በቁልቢ እና በሐዋሳ ከተሞች በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በየአመቱ ሐምሌ 19 ቀን የሚከበረው የገብርኤል አመታዊ ንግሥ በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ተከናወነ። የክብረ በዓሉ ታዳሚዎች ቁጥር በቁልቢ ሲጨምር በሐዋሳ በግማሽ ገደማ መቀነሱን የጀርመን ራድዮ ዘግቧል።
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቁልቢ ከተማ የተካሔደው የዛሬው የበዓል አከባበር ምንም እክል እንዳልገጠመው የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ኃላፊ ኮማንደር ሱልጣን አወል ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

https://telegra.ph/HAMLE19-07-26
#ATTENTION

#ቁልቢ_ገብርኤል_ንግስ_በዓል

የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከነገ ታኅሣሥ 15/2013 ጀምሮ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ድረስ ባለው ዋናው መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪዎች አቁሞ መሄድ እና መተላለፍ አይቻልም ተብሏል።

መልዕክት ለምእመናን ፦

ማንኛውም ዓይነት ወንጀል ሲፈጸም እንዲሁም ወድቆ የተገኘ ንብረትና ገንዘብ ሲገኝ ቁልቢ ገብርኤል ገዳም ለሚገኘው ጊዜያዊ የፖሊስ ጣቢያ በስልክ ቁጥር 0253390335 ደውለው ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብር እንድታደርጉ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ቁልቢ

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓልን ለማክበር ወደ ስፍራው የሚመጡ ምዕመናንና እንግዶችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ዝግጅት ማድረጉን ፖሊስ አሳውቋል።

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ እና የበዓሉ የጸጥታ ኮማንድ በመጪው ረቡዕ በሚከበረው ዓመታዊ የቁልቢ ንግስ በዓል ላይ ከተለያየ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ብዛት ያላቸው ምዕመናን፣ ቱሪስቶችና ሌሎችም እንግዶች ወደ ስፍራው እንደሚመጡ ይጠበቃል ብለዋል።

የምዕመናኑን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅም ከምዕራብ ሐረርጌ ዞን ፣ከድሬዳዋ አስተዳደር፣ ከሐረሪ ክልል እና ከፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊት፣ ብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ጋር በመቀናጀት ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል።

የበዓሉ ታዳሚዎች የግል ንብረቶቻቸውን እንዳይሰረቅ በጥንቃቄ በመያዝና የወንጀል ድርጊት ሲመለከቱ በማጋለጥ የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ተብሏል።

በንግስ በዓሉ ላይ ሶስት ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያና ተጠርጣሪ ወንጀለኞችም ሲያዙ ውሳኔ ለመሰጠት ዐቃቤ ህግና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል።

ወደ ስፍራው በሚያመራው መንገድ አልፎ አልፎ ያለው አካባቢ የመሬቱ አቀማመጥ ዳገታማ፣ ቁልቁለታማና ጠመዝማዛ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግና ደንብ በማክበር አደጋን ለመከላከል የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።

ከዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ባለው ዋናው የተሸከርካሪ መንገድ ላይ #ከባድ_መኪና ማለፍ የተከለከለ መሆኑንም ተገልጿል።

ምዕመናን ወደ ንግስ ስፍራው በሚመጡበት ወቅት ተገቢነት የሌላቸው አርማና ምልክቶችን ይዘው መገኘት እንደሌለባቸውም ፖሊስ አሳስቧል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #ቁልቢ #ሀዋሳ

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓልን ተከትሎ ፤ ከታህሳስ 17 እስከ ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰዓት ባሉት ቀናት ከጨለንቆ እስከ ቀርሳ ባሉት ከተሞች ዋና መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል ነው ተብሏል።

ታህሳስ 19 የሚከበረው ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ጊዚያዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል አሳውቀዋል።

ለበዓሉ የሚያቀኑ አሽከርካሪዎች አካባቢው ዳገት፣ ቁልቁለት እና ጠመዝማዛ መንገድ ስለሚበዛው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የትራፊክ ህግና ደንብ አክብረው እንዲያሽከረክሩ ማሳሰቢያ ተለልፏል።

ከታህሳስ 17 እስከ ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰዓት ባሉት ቀናት ከጨለንቆ እስከ ቀርሳ ባሉት ከተሞች ዋና መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪ ፦

- የጸጥታ አካላት ቋሚና ተንቀሳቃሽ ጥበቃ እያደረጉ ይገኛሉ።

- በበዓሉ ወቅት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ሲያዙ ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት እንዲቻል ጊዜያዊ ፍርድ ቤት በአቅራቢያ ተቋቁሟል።

- ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያዎች ተቋቁሟል።

የበዓሉ ታዳሚዎች ንብረቶቻቸውን #በጥንቃቄ እንዲይዙ መልዕክት ተላልፏል። ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳይ ካጋጠመ በአቅራቢያ ላለ የፀጥታ አካል ጥቆማ መስጠት ይቻላል።

በተመሳሳይ ፤ በሀዋሳ ለሚከበረው የቅዱስ ገብርዔል ዓመታዊ የንግስ በዓልን አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉ ተነግሯል።

ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ብሎም ደህንነታቸው ተጠብቆ በከተማዋ ውስጥ መንቀሳቀስ እንዲችሉ ሁሉም አካል በትብብር እየሰራ ነው ተብሏል።

ስርቆት፣ ያለአግባብ ዋጋ ጭማሪ ፣ ማጭበርበር እንዳይፈፀም የጥንቃቄ ስራ እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደር አሳውቋል።

በዓሉ በሚከበርበት ዕለትና ሥፍራ ወንጀል ተፈፅሞ ቢገኝ አፋጣኝ ፍትህ የሚሰጥ ጊዜያዊ ችሎት መሰየሙ ይፋ ተደርጓል።

@tikvahethiopia