TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የተመን ማሻሻያ‼️

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመን #ማሻሻያ
ማድረጉን አስታወቀ።

የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ #ሽፈራው_ተሊላ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ አዲሱ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመን ከፊታችን ታህሳስ ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ነው።

የዋጋ ንረትና አለም ላይ ያለው የሃይል ተመን ለማሻሻያው ምክንያት መሆናቸውንም ዋና ስራ አስፈጻሚ ተናግረዋል።

አሁን በተደረገው ማሻሻያ መሰረትም ተጠቃሚው ከ12 አመት በፊት በነበረው የሃይል ዋጋ ተመን መሰረት የሚከፍል ይሆናል ነው ያሉት።

በተመኑ መሰረት ተጠቃሚው የወጭውን 25 በመቶ ሲሸፍን ቀሪው 75 በመቶ ደግሞ በመንግስት ድጎማ የሚደረግበት ነው ተብሏል።

ማሻሻያው በሰባት እርከኖች የተከፈለ ሲሆን፤

እርከን 1: እስከ 50 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በነበረው ክፍያ በኪሎ ዋት 0 ነጥብ 2730 ብር ይቀጥላል፤

እርከን 2: እስከ 100 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 0 ነጥብ 6644 ብር የነበረው በአዲሱ ተመን 0 ነጥብ 7670 ብር፤

እርከን 3: እስከ 200 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 1 ነጥብ 3436 ብር የነበረው በአዲሱ ተመን 1 ነጥብ 6250 ብር፤

እርከን 4: እስከ 300 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 1 ነጥብ 6375 ብር የነበረው በአዲሱ ተመን 2 ብር፤

እርከን 5: እስከ 400 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 1 ነጥብ 7917 ብር የነበረው በአዲሱ ተመን 2 ነጥብ 2000 ብር፤

እርከን 6: እስከ 500 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 1 ነጥብ 9508 ብር የነበረው በአዲሱ ተመን 2 ነጥብ 4050 ብር እንዲሁም

እርከን 7: ከ500 ኪሎ ዋት በላይ ለሚጠቀሙ ከዚህ ቀደም በኪሎ ዋት 2 ነጥብ 0343 የነበረው በአዲሱ ተመን 2 ነጥብ 4810 ብር ይሆናል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia