TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና‼️

በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን #ያአበሎ_ወረዳ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።

የተሽከርካሪ አደጋው ያጋጠመው ከኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያአበሎ ከተማ ወደ ደቡብ ክልል #ኮንሶ ከተማ #ኮንትሮባንድ_ጭኖ በፍጥነት ሲጓዝ የነበረ ተሽርካሪ ከተቃራኒ አቅጣጫ ከሚመጣ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በያአበሎ ወረዳ ኛሮ ቀበሌ ኤላ ዲማ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋም ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን ከቦረና ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክተታል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia