TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የተቃውሞ ሰልፉ ሳይካሄድ ቀረ‼️

በቅርቡ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የጸደቀውን የስደተኞች አዋጅ #በመቃወም በጋምቤላ ክልል ተወላጆች ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው ሰልፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ ሳይካሄድ ቀርቷል። ረፋድ 3፡30 ገደማ ከ35 እስከ 40 የሚሆኑ የጋምቤላ ክልል ተወላጆች በመስቀል አደባባይ ቢሰባሰቡም ፍቃድ ያገኙበትን ደብዳቤ ለጸጥታ አስከባሪ ፖሊሶች ማቅረብ ባለመቻላቸው ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል። የጸደቀው አዋጅ በጋምቤላ ክልል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩ እና፣ ህዝቡ ተወያይቶ #መግባባት ላይ ያልደረሰበት መሆኑ ሰልፍ ለማድረግ እንዲነሳሱ እንዳደረጋቸው በቦታው የጀርመን ድምፅ ራድዮብያነጋገራቸው ወጣቶች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ሊካሄድ የነበረው ሰልፍም የከተማ አስተዳደሩ አሁን ያለው የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስችል ባለመሆኑ ፈቃድ አልሰጥም በማለቱ አለመከናወኑን የጀርመን ድምፅ ራድዮ በስልክ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪ #አረጋግጠዋል

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጥለቻ ንግግር ወጊውን መልሶ #ይጎዳል!
(በሚራክል እውነቱ)

የጥላቻ ንግግር የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በፖለቲካዊ አመለካከት፣ በሚከተሉት እምነት፣ በዘር፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሃብት ደረጃ በቀለማቸው በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእኛ ሃሳብ ተቃራኒ ናቸው ብለን የምንፈርጃቸውን ሰዎች ስብእናቸውን በመጋፋት፣ ማንነታቸውን ጭምር በሚያሳንስና በሚያዋርድ መልኩ የሚሰነዝር ቃል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ሰዎችን በማይሆን ፍረጃ ይገደል ይታሰር ይሰደድ የሚል ፍርድ በማሳለፍ ጭምር ሚዛናዊነትን የሚያስት ነው የጥላቻ ንግግር፡፡ እከሌ እንዲህ ካልሆነ፤ እክሌ ይሄ ፍርድ ይገባዋል፣ እክሌ ንፁህ ነው፤ ይሄኛው ደግሞ በደሉ ክልክ በላይ ሆኗል፤ ይሄ ወገን ይሄ ፍርድ ይገባዋልና መሰል የጥላቻ መርዞችን በመርጨት የሰዎችን አብሮ የመኖር እሴት እንዲሸረሸር የማድረግ አባዜ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ የሚሰነዘር የጥላቻ ንግግር የሰዎችን ስብዕና በመጋፋት ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ጠንካራ ስነልቦና ያለው ሰው እንኳን በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ ክብረ ነክ በሆኑ የጥላቻ ንግግሮች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ የዚህን ትርፍና ኪሳራ መመዘን እንግዲህ የባለቤቱ ነው፡፡

ማንም ሰው ወደዚህ ምድር የመጣው በምክነያት ነው፡፡ እኔ የተፈጠርኩት በምክንያት ነው ብሎ ማመን ግድ ይላል፡፡ ያኔ እያንዳንዳችን በምንዘራው ልክ የምናጭድ መሆናችን ይገባናል፡፡ በጎ በጎውን ተናግሮ ተፅእኖ መፍጠርና የተሳሳተ አስተሳሰብ ማራመድና የጥላቻ ንግግር የሚያመጣውን መመዘን ይገባል፡፡

በመሆኑም በግለሰቦች ወይም በህዝቦች መካከል አለመግባባት፣ ብሎም #ግጭትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ የጥላቻና #አደገኛ ንግግሮች መባባስ የማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ አስተዋጽኦ በእጅጉ የጎላ መሆኑ እርግጥ ነው በመሆኑም የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላል ማለት ነው፡፡

ማህበራዊ ሚዲያዎች ማህበረሰቡን ለሚጎዱ መጥፎ ተግባራት ማራመጃነት እንዳይውሉ ይልቁንም ለአገር #ሰላምና የጋራ #መግባባት በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሁሉም ከራሱ ጀምሮ ከጥላቻ ንግግር ራሱን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ መጨረሻው ለራስ የሚኖር ግምት ያነሰ እንዲሆን በማድረግ ራስን ጭምር ለማህበራዊ ቀውስ የሚከት ነውና፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia

“አረና” የመገንጠል አላማ ያላቸውን ሃይሎች አጥብቄ እታገላለሁ አለ!

በትግራይ የተለየ አስተሳሰብን የማፈን እንቅስቃሴ እንዲቆም ጠይቋል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተቀነቀኑ ያሉ ፀረ አንድነት ዘመቻዎችን እቃወማለሁ ያለው አረና ትግራይ ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፤ በትግራይ የመገንጠል አላማ ያነገቡ አደረጃጀቶች መበራከታቸው አሳሳቢ ነው ብሏል፡፡ 

ፓርቲው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው መግለጫ፤ የትግራይ ክልል ህዝብን ከሌሎች ክልል ህዝቦች ጋር ለማጋጨት በመንግስታዊ ሚዲያዎችና በማህበራዊ ድረ ገፆች ጥረት እየተደረገ መሆኑን በመጠቆም፤ በማንኛውም መልኩ ህዝቦችን ለማጋጨት የሚደረጉ ጥረቶችን በጥብቅ እንደሚያወግዝ አስታውቋል፡፡ 

#በጥላቻና ባልተገቡ ዘመቻዎች #መፈናቀል የደረሰባቸው የትግራይ ተወላጆች እርቅ ተፈጽሞ ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ የጠየቀው አረና፤ የወሰን ጥያቄዎችም #በውይይትና #መግባባት መፈታት እንዳለባቸው ገልጿል፡፡ 

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/AA-08-06-2
#update ኬንያና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ወደ ወደ ሰላማዊ ሁኔታው ለመመለስ ተስማሙ፡፡ ኬንያና ሶማልያ በህንድ ውቅያኖስ ጠረፍ ስፍራ ይገባኛል ውጥረት ውስጥ ገብተው ለወራት ዘልቀዋል፤ ጉዳዩንም ዘ ሄግ ለሚገኘው ዓለማቀፍ ፍርድ ቤት አቅርበዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ግንኙነታቸውን ለማሻሻል #መግባባት ላይ መድረሳቸው ተሰምቷል፡፡ በግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ አሸማጋይነት በተደረገ ምክክር የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሀሳብ ማዕድ!

#ማዳመጥ #መረዳት #መናገር #መግባባት

በዓለማቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት አዘጋጅነት የሚካሄደው ሁለተኛው የአክቲቪስቶች የውይይት መድረክ በቀነኒሳ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የሚዲያ ባለሞያዎች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በውይይቱ መጀመሪያ ላይ አዘጋጁ እንደተናገረው ተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎችና አክቲቪስቶችን አቀራርቦ ማወያየት የዝግጅቱ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ዶ/ር አደረ አብደላ እንደገለጹት በአክቲቪስቶች መካከል በመደማመጥ ላይ ያተኮረ ሁሉም ሃሳቡን በእኩል ማካፈልና ከተቻለ የጋራ መግባባትን መፍጠር ካልሆነም ልዩነቶችን አቻችሎ ለሀገር ደህንነትና ሰላም በጋራ መቆም ይኖረባቸዋል ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ሌሎች እንዲያደምጡን ብቻ ሳይሆን እኛም ሌሎችን ማድመጥ የምንችልበትን መድረክ ማመቻቸት የዚህ ዓላማ ዋነኛው ዓለማ ነው በማለት አክለው ገልጸዋል፡፡ ፕሮግራሙ አካታች ለማድረግ ጥረት የተደረገ ሲሆን በዚህ ውይይት 12 አክቲቪስቶች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

በመድረኩ የሚነሱ ሃሳቦችን እየተከታተልን እናሳውቃለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia