TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የጥላቻ ንግግርን በመቃወም ደሜን እለግሳለሁ!

3ተኛው የሲቪል ማህንዲሶች ቀን ከትላት አርብ ጀምሮ እስከ እስከ ነገ እሁድ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ አዘጋጅነት እየተከበረ ይጋኛል፡፡ በትላንትናው መርኃግብር ላይ የግጥም ውድድር የተካሄደ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የአስፉልት ላይ ሩጫና የደም ልገሳ ይደረጋል፡፡ በመዝጊያው ቀን እሁድ የመምህራን እና የተማሪዎች የእግር ኳስ ጫወታ፣የፓናል ውይይትና የፈጠራ ሥራ ውድድር በቴክኖሎጂ ተማሪዎች መካከል ይደረጋል፡፡ በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስቴዲየም እንደሚካሄድ የወጣው መርኃግብር ያሳያል፡፡ በዛሬው ዕለት በሚካሄደው የደም ልገሳ ላይ የወላይታ ሶዶ #stop_hate_speech_movement አባላት #የጥላቻ_ንግግርን_በመቃወም_ደም_እንለግሳለን በሚል መሪ ቃል ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሲቪል ምህንድስና ተማሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅተዋል፡፡

Via #Bereket
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የተገነባ ህንጻ በሁለት ሰዓት ይፈርሳል እኛ ግን የማይፈርሰውን የአስተሳሰብ ለውጥ መገንባት ይገባናል፡፡" ፕ/ር ታከለ ታደሰ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት

"የ15 ደቂቃ የንባብ ልምድ ሀገርን ይለውጣል፡፡.....እኔ አንበሳ ስባል አልወድም ጅብ መሆን ነው ምኞቴ ምክንያቱም አንበሳ 20ሰዓት ይተኛል እኔ ግን 20 ሰዓት ማንበብ ፈልጋለሁ፡፡" ደራሲ ዘነበ ወላ

ዛሬ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በተዘጋጀው ሁለተኛው የንባብ ቀን የተላለፉ መልዕክታት ናቸው፡፡ የመርኃ-ግብሩ መሪ ቃል የንባብ ልምድ ለአስተሳሰብ ልህቀት የሚል ሲሆን ዝግጅቱን በበላይነት የሶሻል ሳይንስ የወላይትኛ ቋንቋ ት/ክፍል አዘጋጅቶት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የተሳተፉበት ነበር፡፡

Via #Bereket
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር #ጀማል_አባፊጣ👆

#የStopHateSpeech የሁለት ቀን መድረክ በይፋ ተጀምሯል። በመጀመሪያው ቀን መድረክ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ተገኝተዋል። "ጅማ የመቻቻል የፍቅር የአንድነት ተምሳሌት ናት። የጅማ ሰው ሲመርቅ ቡናና ሰላም ከቤትህ አይጥፋ ይላል። ጥላቻ #ቆሻሻ ነው እራሳችንን ከዝህ ተግባር እንቆጥብ" የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። በከሰዓቱ መርሃግርብር በወጣት ተማሪዎች መካከል ስለጥላቻ ንግግር ውይይቶች ይደረጋሉ።

Via #Bereket
@tsegabwolde @tikvahethiopia