TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#WANTED #ተፈላጊ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በ ' ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ' በቀራንዮ ንዑስ ከተማ ታህሳስ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 አካባቢ የፍቅር ጥያቄ አቅርቦ አለመግባባት በመፈጠሩ ምክንያት ተጠርጣሪው አቶ ይኸነው ፈንታ ይሁኔ የተባለ ግለሰብ የፍቅር ጥያቄ ባቀረበላት ወጣት ፊት እና ሌሎች የሰውነት ክፍሏ ላይ አሲድ በመድፋት ከፍተኛ አካላዊ ጉዳት በማድረስ ከአካባቢው ተሰውሯል፡፡

የወረዳው ፖሊስም ወንጀሉ ከተፈፀመበት ሰዓት ጀምሮ ተጠረጣሪ ወንጀለኛውን ለመያዝ ክትትል እያደረገ የሚገኝ ቢሆንም አሁንም በቁጥጥር ሥር አልዋለም።

ስለሆነም ተጠረጣሪ ግልሰቡ ያለበትን አካባቢ ለፖሊስ ትብብርና ጥቆማ በመስጠት በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውል ህዝቡ እገዛ እንዲያደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ስልክ ቁጥር ፡ 058 661 02 01

" ወንጀል ሠርቶ ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም "

( በምስራቅ ጎጃም ዞን የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ፖሊሲ ጽህፈት ቤት )

#ሼር #Share

@tikvahethiopia