TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሪፖርት

ከቀናት በፊት የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ ታጣቂዎች በአማራ ክልል ውስጥ የፈፀሟቸውን ግፎች በሪፖርቱ ያሳወቀው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትላንት ሌላ ኢትዮጵያን የሚመለከት ሪፖርት ይዞ ወጥቷል።

ይኸው ሪፖርት በአዲስ አበባ ከተማ የትግራይ ተወላጆችን ትኩረት ያደረገ እስር እየተካሄደ መሆኑን የሚገልፅ ነው።

አምነስቲ በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ ጉዳይ ሪፖርት ሲያቀርብ ይህ 2ኛው ነው።

አምነስቲ በትላንት ሪፖርቱ በአ/አ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠረ እስር እየተካሄደ ነው ፤ እስሩ የተባባሰው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኃላ መሆኑን ገልጿል።

ሰዎች ከቤት ወደ ቤት በሚደረግ አሰሳ በቁጥጥር ስር ይውላሉ ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የፖሊስ ጣቢያዎች በመሙላታቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ የመንግስት ሰራተኞች፣ የኦርቶዶክስ ቄስ እና የህግ ጠበቃን ጨምሮ ሌሎች እስረኞች በወጣቶች ማእከላት እና ሌሎች መደበኛ ባልሆኑ የማቆያ ጣቢያዎች ታስረዋል ብሏል አምነስቲ ኢንተርናሽናል።

ሙሉ ሪፖርቱ : https://www.amnesty.org/en/latest/news/2021/11/ethiopia-tigrayans-targeted-in-fresh-wave-of-ethnically-motivated-detentions-in-addis-ababa/

ከቀናት በፊት #ኢሰመኮ በአ/አ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀ ጀምሮ ሰዎች ከስራ ቦታቸው፣ ከመኖሪያ ቤታቸው እና ከመንገድ ላይ ጭምር በቁጥጥር ስር ውለው በተለያዩ የከተማዋ ፖሊስ ጣቢያዎች ተይዘው እንደሚገኙ አረጋግጫለሁ ሲል ሪፖርት ማድረጉ አይዘነጋም።

ኢሰመኮ እስሩ ማንነት/ብሄርን መሰረት ባደረገ መልኩ በሚመስል ሁኔታ መከናወኑን ማሳወቁ ይታወሳል ፤ (ምንም እንኳን በግልፅ እስሩ የቱን ብሄር መሰረት እንዳደረገ ባይገልፅም) ።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዛሬ የዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ነው።

አካል ጉዳተኞችን እንደተረጂ ማየት ትክክል አይደለም!

አካል ጉዳተኞችን በህክምና እንዴት ማስተካከል ወይም ማከም እንደሚቻል ብቻ ማሰብ ትክከለኛ አመለካከት አይደለም!

#ዓለም_አቀፍ_የአካል_ጉዳተኞች_ቀን ዘንድሮ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለ29ኛ ጊዜ እና በዓለም ለ30ኛ ጊዜ “የአካል ጉዳተኞችን መሪነትና ተሳትፎ ለማረጋገጥ አካታች፣ ተደራሽ እና ዘላቂ ድህረ ኮቪድ-19 ዓለምን እንገንባ” በሚል መሪ ቃል በጅግጅጋ እየተከበረ ይገኛል።

#ጤናማቃላት #ኢሰመኮ #ሁሉንምያካተተ

@tikvahethiopia
#EHRC

ነጻነታቸውን በተነፈጉ ሰዎች መብቶች ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ምርመራ ይካሄዳል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን /ኢሰመኮ/ ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው ድጋፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ብሔራዊ ምርመራ (National Inquiry) ለማካሄድ ከፌዴራልና ከ9 ክልሎች የተወጣጡ የፖሊስ ኮሚሽነሮች ፣ የፍትሕ ተቋማት ተወካዮች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የማስጀመሪያ ዓውደ ጥናት አድርጓል።

ኮሚሽኑ ይህን አይነት ሀገራዊ ምርመራ ለማድረግ ሲጀምር የመጀመሪያው ነው።

ፕሮጀክቱ ለ3 ዓመት የሚቆይ ሲሆን 15 ሚሊዮን ዩሮ በጀት ተይዞለታል። ይህም የወንጀል ፍትሕ አስተዳደርን ሪፎርም ለማድረግ እየተቀረጸ ያለው ፕሮግራም አንዱ አካል መሆኑ ተገልጿል።

• ሀገራዊ ምርመራ ምንድን ነው ?

• 'ነጻነታቸውን የተነፈጉ ሰዎች' ስንል ምን ማለታችን ነው ?

• ከሀገራዊ ምርመራው ምን ይጠበቃል ? ምንስ ተግዳሮቶች አሉት ?


ያንብቡ : https://telegra.ph/ኢሰመኮ-02-17
TIKVAH-ETHIOPIA
ያላየነው ብዙ ጭካኔ ይኖር ይሁን ? በርካቶች በጋምቤላ ተቀርፆ በተሰራጨው ጨካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ቪድዮ የተሰማቸውን ሀዘን በአግባቡ ሳይወጡ ዛሬ ደግሞ አንድ ቀኑ ሆነ አድራሻው የት እንደሆነ የማይታወቅ የጅምላ ርሸና ቪድዮ ተሰራጭቷል። ለጊዜው ድርጊቱ መቼ .. ? የት ? እንዴት ? ተፈፀመ ስለሚለው ማወቅ ቢያዳግትም ከዚህ ቀደም እንዳየናቸው እጅግ በጣም ዘግናኝ እና ህጋዊ ያልሆነ የጭካኔ ተግባር…
#UPDATE #EHRC

በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀው ቪድዮ

" ... በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የሚታየው ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኢሰመኮ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ሪፖርት ላይ የተካተተ ነው።

የኢሰመኮ የምርመራ ሪፖርት ከምስክሮች እና በስፍራው በመገኘት በመስክ ምልከታ ያሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ፣ ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) መፈጸሙን፤ እንዲሁም በወቅቱ በነበረው መረጃ መሰረት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

ኢሰመኮ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ከተመለከተ በኋላ ባደረገው ተጨማሪ ማጣራትና የቴክኒክ ምርመራ፣ በመስክ ምርመራ በለየው ስፍራና በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ያለውን ስፍራ በቴክኒክ ምርመራ በማነጻጸር፣ እንዲሁም ምስሉ የተቀረጸበትን ቦታ ለማነጻጸርና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የቴክኒክ ምርመራዎችን በማድረግ፤ ከዚህ በላይ የተገለጸው በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል "

#ኢሰመኮ

@tikvahethiopia
#የምርመራ_ሪፖርት

በኦሮሚያ ክልል ፤ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ፤ " ጎቡ ሰዮ ወረዳ " አኖ ከተማ በጥር 25 ቀን 2015 ዓ.ም. በዋናነት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ኢላማ በማድረግ ጥቃት የተፈፀመ ሲሆን ይህ በተመለከተ #ኢሰመኮ ምርመራ አድርጓል።

ምርመራውን በተመለከተ ከላከልን መግለጫ ፦

- ጥር 25/ 2015 ዓ.ም. ከንጋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው የወታደር ልብስ የለበሱ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) መሆናቸው በነዋሪዎች የተገለጹ ታጣቂዎች በ3 አቅጣጫ ወደ " አኖ ከተማ " መግባታቸውን፤ በመቀጠል በከተማዋ የተለያዩ አቅጣጫዎች ተከታታይ የሆነ የተኩስ ድምፅ መሰማት መጀመሩን እና የሲቪል ሰዎች ግድያና የአካል ጉዳት፣ የንብረት ዘረፋ እና ውድመት መድረሱ ታውቋል።

- በጥቃቱ ዋና ኢላማ የተደረጉት ከ " ጎቡ ሰዮ ወረዳ " የተለያዩ ቀበሌዎች ተፈናቅለው በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች የተጠለሉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ናቸው።

- በታጣቂ ቡድኑ በተፈጸመ ጥቃት አንድ የክልል የሥራ ኃላፊ ከነሾፌሩ፣ የከተማ ፖሊስ እና የቀበሌ ሚሊሻ አባላትን ጨምሮ ቢያንስ ሃምሳ (50) ሰዎች ተገድለዋል። ከእነዚም መካከል 42 ተጎጂዎች በተፈናቃዮች የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ እና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው ይኖሩ የነበሩ ተፈናቃዮች እንዲሁም መንግሥትን ይደግፋሉ የተባሉ ነዋሪዎች ነበሩ፡፡

- ከሟቾች መካከል አራት #ሴቶች እና ሦስት #ሕፃናት ናቸው፡፡

- ታጣቂዎቹ ‘ሰኞ ገበያ’ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ተፈናቃዮችን ቤት ለቤት እየዞሩ በተለይ የአማራ ብሔር ተወላጆችን ለይተው ገድለዋል፡፡

- በከተማዋ ውስጥ የሚገኝ እና ቀደም ሲል የቀበሌ አስተዳደር ንብረት የነበረና ወደ አረጋውያን፣ ሴቶች እና ሕፃናት ተፈናቃዮች መጠለያነት ተቀይሮ በማገልገል ላይ ይገኝ የነበረ ግቢ ውስጥ በመግባት በፈጸሙት ጥቃት፤ በግቢው ውስጥ የነበሩ ማምለጥ ያልቻሉ ወንድ ተፈናቃዮችን መርጠው ገድለዋል። ከእነዚህም መካከል ከተገደሉ በኋላ #ሬሳቸው_በእሳት የተቃጠለ ሰዎች አሉ፡፡ በጥቃቱ ምክንያት ተፈናቃዮቹ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የተበተኑ ሲሆን መጠለያውም በጊዜያዊነት ተዘግቶ ነበር፡፡

- የሟቾችን አስከሬን ጥቃቱ በተፈጸመበት ዕለት እና በማግስቱ የአካባቢው ማኅበረሰብ መቅበሩን የተጎጂዎች ቤተሰቦች አስረድተዋል።

- 8 ሰዎች ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

- በተፈጸመው ጥቃት በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የግለሰቦች የንግድ መደብሮች፣ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አኖ ቅርንጫፍ እና ሌሎች ተቋማት መጠነ ሰፊ ዘረፋ እና ውድመት ተፈጽሞባቸዋል፡፡ 

ሙሉ ሪፖርት ፦ https://publielectoral.lat/c/1370522004/23484

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጋዜጣዊ_መግለጫ : " በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው ሰዎችን አስገድዶ የመሰወር (Enforced Disappearance) ድርጊት በአፋጣኝ ሊቆም ይገባል " - የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን @tikvahethiopia
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎች እየጨመረ የመጣውን የአስገድዶ መሰወር (Enforced Disappearance) እና ተይዘው የሚገኙበት ሁኔታ ሳይታወቅ በእስር ላይ የሚገኙ (incommunicada Detention) ሰዎችን ጉዳይ ሲከታተል ከቆየ በኃላ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

ኢሰመኮ ምን አለ ?

- በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በርካታ የአስገድዶ መሰወርን ድርጊት የሚያቋቁሙ ድርጊቶች መከሰታቸውን ተረጋግጧል።

- አብዛኛውን ጊዜ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆኑ ሰዎች ከመኖሪያ ቤታቸው፣ ከሥራ ቦታ ወይም ከመንገድ ላይ የሲቪልና የደንብ ልብስ በለበሱ የመንግሥት ጸጥታና ደኅንነት ሠራተኞች ያለ ፍርድ ቤት የመያዣ ትእዛዝ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ ወዳልታወቀ ስፍራ እየተወሰዱ እንዲሰወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት፣ ሳምንታት ወይም ወራት መሰወር በኃላ የተገኙ መሆናቸው የተገለጸ ቢሆንም፣ ሌሎች ይህ መግለጫ እስከተሰጠበት ጊዜ ድረስ በግዳጅ እንደተሰወሩ የቀጠሉ ናቸው፡፡

- ከተጎጂዎች መካከል የተወሰኑት ሲያዙ በወንጀል ተጠርጥረው የሚፈለጉ መሆኑ ተነግሯቸው ወደ መደበኛ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰዱ በኋላ የተሰወሩ ሲሆን ከፊሎቹ ደግሞ ምንም ሳይነገራቸው በጸጥታ ኃይሎች ተወስደው የተሰወሩ ናቸው፡፡

ምሳሌ ፦

#1

በአዲስ አበባ ከተማ ከሚያዝያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በማስገደድ ተሰውረው ከነበሩ ሰዎች ውስጥ ከተለያየ የጊዜ መጠን መሰወር በኃላ ወደ ፌዴራል ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው የተገኙ ሲኖሩ፣ አስገድደው በተሰወሩበት ወቅት በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ውስጥ " ገላን " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ የቀድሞው ልዩ ኃይል ካምፕ ውስጥ ተይዘው እንደቆዩ ለማወቅ ተችሏል። በአስገድዶ መሰወሩ ወቅት ተፈጽሟል ስለተባለ ተገቢ ያልሆነ አያያዝ ወይም #የማሰቃየት ተግባር ኮሚሽኑ ምርመራውን ቀጥሏል።

#2

በአማራ ክልል በባሕር ዳር እና በደብረ ብርሃን ከተማ የአስገድዶ መሰወር ሰለባዎች የሆኑ ሰዎችን ጉዳይ ኮሚሽኑ ሲከታተል ቆይቶ ነበር። ከነዚህም ውስጥ አንድ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል " ከሠራዊቱ ከድቷል " በሚል በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወረብ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወላጅ #አባቱን " ልጅህን አምጣ " በሚል ሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በግዳጅ ተወስደው ተሰውረው ከቆዩ በኋላ ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ተለቀዋል፡፡

#3

አንድ የቀድሞ የ " ሶማሊ  ክልል  ልዩ  ኃይል " አባል ታኅሣሥ 6 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ከቢሮ ተደውሎለት ለሥራ ጉዳይ ቢሮ እንዲመጣ ተጠርቶ ከሄደ በኋላ በዕለቱ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ጅምሮ ስልኩ የተዘጋ ሲሆን ከዚያ ቀን ጀምሮ የት እና ምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ለማወቅ አልተቻለም፡፡

#4

ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቦታዎች ቢያንስ #ሰባት ሰዎች የአስገድዶ መሰወር ድርጊት ሰለባ መሆናቸው ለኢሰመኮ አቤቱታ ቀርቦ ክትትል እየተደረገባቸው ነው።

ከእነዚህ መካከል በምዕራብ ወለጋ ዞን ጎቡ ሰዮ ወረዳ ነዋሪ የሆነ አንድ ሰው ይገኝበታል፡፡

ይህ ግለሰብ ግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. በወረዳው ፖሊስ ከሌሎች ሦስት ጓደኞቹ ጋር ተይዞ ፖሊስ ጣቢያ ከገባ በኋላ ሰኔ 9 ቀን 2014 ዓ.ም. ከሌሎቹ ታሳሪዎች ተለይቶ ነቀምት ከተማ የሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ መዘዋወሩ ለቤተሰብ የተነገረ ቢሆንም ከዚያ ቀን ጀምሮ ያለበትን ቦታ እና ሁኔታ ማወቅ አልተቻለም፡፡

በተመሳሳይ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የምሥራቅ ወለጋ ዞን የኦፌኮ አስተባባሪ የሆነ ሌላ ሰው ጥቅምት 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት አካባቢ ላይ ከሚሠራበት መሥሪያ ቤት በመንግሥት #የደኅንነት_ኃይሎች ተይዞ ነቀምት ከተማ በሚገኘው የጸጥታ ቢሮ ውስጥ ታስሮ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት እንደነበረና እጁ በሰንሰለት በመታሰሩ ምክንያት ከቤተሰብ የሚሄድለትን ምግብ ተቀብሎ መመገብ ሲያቅተው ሰዎች የተመለከቱት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

ግለሰቡ ከጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ሊገኝ አልቻለም።

ቡራዩ በተለምዶ " አሸዋ ሜዳ " ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊሶች ተይዞ በቡራዩ ወረዳ 3 ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር ውሎ የቆየ አንድ ሰው ከሁለት ወራት የፖሊስ ጣቢያ ቆይታ በኋላ አንድ ቀን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ (ቀነ በትክክል አልታወቀም) ከሌሎች እስረኞች ተለይቶ መወሰዱ የታወቀ ቢሆንም ፣ ከዚያን ቀን ጀምሮ ያለበትን ቦታ እና ሁኔታ ማወቅ አልተቻለም፡፡

ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ቁጥራቸው ከሃያ ያላነሱ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በሰሜን ሸዋ ዞን ፣ ሱሉልታ ወረዳ ፣ ለገጦ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ፣ ልዩ ስሙ " ረቡዕ ገበያ " ፣ 04 ቀበሌ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ በመምጣት አንድ ሰው ይዘው የሄዱ ሲሆን፤ በማግስቱ ቤተሰቦቹ ታሳሪውን ለመፈለግ ወታደሮቹ ይኖሩበት ወደነበረው ደርባ ቶኒ፣ አበባ ልማት ካምፕ ቢሄዱም ወታደሮቹ የተያዘው ግለሰብ ያበትን ሁኔታ ሊያሳውቁ ፍቃደኛ አለመሆናቸውን፤ ይልቁንም ለመጠየቅ የሄዱ ሰዎች እስር እና ማስፈራርያ የደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የተያዘው ግለሰብም እስከ አሁን ድረስ ያለበት ሁኔታ እና ቦታ ማወቅ አልተቻለም፡፡

(ሙሉ መግለጫው በዚይ 👉 https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/78928?single ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮች_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት.pdf
3.8 MB
#ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 2ኛውን በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ላይ የሚያተኩር ዓመታዊ ሪፖርት በቀናት በፊት ይፋ አድርጓል፡፡

በሪፖርቱ ምን አለ ?

- ዜጎችን ከመደበኛ የመኖሪያ ቦታቸው ያፈናቀሉ፣ የሰው ሕይወት ያጠፉ፣ ሀብት ያወደሙ፣ አካላዊ ጉዳት ያደረሱ ቡድኖችና ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ በቂ ዕርምጃዎች ባለመወሰዳቸው የሕግ በላይነት፣ ተጠያቂነትንና የተፈናቃዮችን ፍትሕ የማግኘት መብት የሚነፍግ ነው።

- በዘፈቀደ ለሚደረጉ የማፈናቀል ድርጊቶች አስተማሪ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ አይደሉም።

- ዘላቂ የመፍትሔ አማራጮች አተገባበርም የመፈናቀል ምክንያት የሆኑትን የደኅንነት ሥጋቶች ባስወገደ፣ ተፈናቃዮችንና ተቀባይ ማኅበረሰብን ባሳተፈ፣ የተፈናቃዮችን ፍላጎት ባገናዘበ፣ እንዲሁም ተፈናቃዮችን በዘላቂነት በሚያቋቁም ሁኔታ ባለመሆኑ፣ ለዳግም መፈናቀል የሚያጋልጥ ነው።

- አብዛኛዎቹ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ሳያገኙ በመጠለያ ጣቢያዎችና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው መኖር ከጀመሩ በትንሹ ሦስት ዓመታት አልፏቸዋል።

- ተገቢው ጥበቃ የማይደረግላቸው፣ እንዲሁም የሲቪልነት ባህሪን ያልጠበቁ በወታደራዊ ካምፖች አካባቢ የሚኖሩ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው መጠለያ ጣቢያዎች መኖራቸው፣ የተፈናቃዮች የደኅነነት ሁኔታ አደጋ ላይ መሆኑን እንደሚያሳይ፣ በተጨማሪም መንግሥት በካምፓላ ስምምነት መሠረት የተጣለበትን ግዴታ በአግባቡ አለመወጣቱን የሚጠቁም ነው።

- መንግሥት ፈርሞ የተቀበለውን የካምፓላ ስምምነትን ለማስፈጸም የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ፀድቆ ሥራ ላይ አለመዋሉና የተፈናቃዮችን ጉዳይ በባለቤትነት የሚያስተዳድር ተቋማዊ አደረጃጀት የለም።

- መፈናቀልን ለመከላከል ለተፈናቃዮች የሚደረጉ የጥበቃና ድጋፍ ሥራዎች፣ እንዲሁም የዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግ ሒደቶች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች አሁንም አሳሳቢነታቸው ቀጥሏል።

- የተፈናቃዮች ምዝገባና ሰነድ የማግኘት ሥርዓቱ ላይ ያለው ክፍተት ለተፈናቃዮች የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ እንዳይከናወን አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። በተጨማሪ ተፈናቃዮች ሌሎች የመንቀሳቀስና የማኅበራዊ አገልግሎት የማግኘት መብቶቻቸውን ለመጠቀም እንዳይችሉ አድርጓል።

- በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆነው መፈናቀል ኃይል በተቀላቀለባቸው ግጭቶች ምክንያት የሚከሰት በመሆኑ መፈናቀልን ለመከላከልና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት፣ በዋናነት ግጭቶችን ወቅታዊ በሆነ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያስፈልጋል፡፡ #ሪፖርተር

(ከኢሰመኮ የተላከ ሙሉ ሪፖርት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ : ለወራት የቀጠለው የትጥቅ ግጭት ዐውድ እና አሉታዊ የሰብአዊ መብቶች እንድምታው " ተፋላሚ ኃይሎች ሲቪል ሰዎችንና ንብረቶችን፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን እና መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ከማድረግ ሊቆጠቡ፣ መንግሥት የማኅበራዊ አገልግሎቶች እዲቀጥሉ አስቻይ ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል። " በአማራ ክልል ጉዳይ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። መግለጫው በክልሉ በተለያዩ…
#አማራ

በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል።

ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል።

በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎችና ወረዳዎች በአንድ ወቅት ላይ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በሌላ ወቅት ደግሞ በታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የትጥቅ ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር / ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው።

በግጭቱ ዐውድ ውስጥ #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው ለመሸሽ ተገደዋል።

ለምሳሌ ፦

- በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ ' መጥተህ ብላ ' ከተማ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ዓመት ከሰባት ወር ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች #ተገድለዋል፤ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- በደብረ ማርቆስ ከተማ ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት  ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

- በደንበጫ ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት ሲቪል ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል።

ኮሚሽኑ እነዚህን መረጃዎች ያገኘው የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የዓይን ምስክሮችን በማነጋገር ነው።

በአንዳንድ አካባቢዎች ጥቃትን አልያም ግጭትን በመሸሽ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ ከቀያቸው ተፈናቅለው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል።

በምንጃር ወረዳ ውስጥ የአውራ ጎዳና ጎጥ ነዋሪዎች ከመስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከቀያቸው ተፈናቀለው ቢያንስ 3ዐዐዐ የሚሆኑት አሞራ ቤቴ ቀበሌ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤትና ክፍት ሜዳ ላይ (በዛፍ ሥር) ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቀ መተሃራና አዋሽን ጨምሮ ወደ የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለዋል።

ለተፈናቃዮች የተወሰነ ድጋፍ በማኅበረሰቡና እና በአንድ ተራድዖ ድርጅት የተደረገ ቢሆንም፣ በቂ ባለመሆኑ በአሳሳቢ ሁኔታ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።

የነዋሪዎችን መፈናቀል ተከትሎ ሰብላቸው እንደወደመ፣ ንብረታቸው እንደተዘረፈ፣ የቤቶቻቸው ጣራያ እና በር እየተነቀለ እንደተወሰደ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ቤቶቻቸውን ከአጎራባች ክልል በመጡ ኃይሎች በኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ጭምር ማፍረስ እንደተጀመረ ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግሥት ኃላፊዎች አስረድተዋል።

በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት የሚፈጸሙ ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎች አሁንም መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ተዓማኒ መረጃዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልጿል።

ግጭቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦

- " ፋኖን ትደግፋላችሁ "

- " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "

- " መሣሪያ አምጡ "


- " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች ተገኝተዋል።

እንደማሳያ ፦

▪️በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2016 ዓ.ም. #ሦስት_ወንድማማቾችን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️በሰሜን ጎጃም ዞን፣ አዴት ከተማ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ፍልሰታ ደብረ ማሪያም የሚኖሩ 12 የአብነት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️ በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ አማኑኤል ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች በቤት ለቤት ፍተሻ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

▪️በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ፣ ግንደወይን ከተማ ሞጣ በር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አንድ በጥይት የቆሰለን ግለሰብ እናቱና እህቱ በባጃጅ አሳፍረው ወደ ሕክምና ተቋም በመውሰድ ላይ እያሉ፣ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባጃጁን አስቁመው ሁሉንም ተሳፋሪዎች ካስወረዱ በኋላ " የቆሰለው እኛን ሲዋጋ ነው " በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪውን ጨምሮ አራቱን ሰዎች በጥይት እንደገደሏቸው ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች አስረድተዋል።

በባሕር ዳር፣ በፍኖተሰላም፣ በጎንደር እና በወልድያ ከተሞች በትጥቅ ግጭቱ ቆስለው ሕክምና ሲከታተሉ የነበሩ የተወሰኑ ሲቪል ሰዎች እና የታጣቂ ቡድኑ አባላት በመሆን በመንግሥት የጸጥታ አካላት የተጠረጠሩ ሰዎች ሕክምናቸው እዲቋረጥ ተደርጎ #ወዳልታወቀ_ስፍራ ከተወሰዱ በኋላ ፣ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ ሕክምና ተቋማቱ ሲመለሱ ቀሪዎቹ ያሉበት ሁኔታ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ማረጋገጥ አልተቻለም።
 
በሌላ በኩል በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች ተፈጽመዋል።

ለምሳሌ ፦

መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ታቦር ሲሄዱ ' አለምበር ከተማ ' አካባቢ በታጣቂዎች ተገድለዋል።

በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ታራሚዎችና ተጠርጣሪዎች እንዲያመልጡ ተደርጓል። 
 
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል ፤ በተለይም ከመንግሥት ተቋማት ጭምር በሚደርሱት መረጃዎች መሠረት በግጭቱ ዐውድ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ድርጊቶች በጣም አሳሳቢ እና በአፋጣኝ ተገቢው ምርመራ ተደረጎ አርምጃ ሊወሰድበት የሚገባው ነው፡፡

የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት በተለያዩ የጤና ተቋማት መድረስ የቻሉትን ተጎጂዎች ቁጥር ብቻ መሠረት በማድረግ ከሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ ቢያንስ #2ዐዐ_የአስገድዶ_መድፈር ተጎጂዎች በጤና ተቋማት ተመዝግበዋል፤ ከተጎጂዎች መካከልም የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሴቶች እና የጤና ባለሞያ ሴቶች ጭምር ይገኙበታል።

ከትጥቅ ግጭቱ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ፦
🔹ሲቪል ሰዎች እና የሲቪል የንግድ እና የመሠረተ ልማት ተቋማት ላይ ዝርፊያ ተፈፅሟል።
🔹የማሳ ላይ ሰብል ውድመት ጨምሮ በሲቪል ሰዎች፣ በሕዝብ እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደርሷል።
🔹ሕፃናት ከትምህርት ውጪ ሆነዋል በአንዳንድ አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት ለወታደራዊ አገልግሎት ውለዋል። ይህ ደግሞ አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ ነው።

በክልሉ ውስጥ በተለየ ሁኔታ ከተፈቀደላቸው ተቋማት በስተቀር ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ የኢንተርኔት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን፣ በተለይም በግጭት ላይ ባሉ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎትም ጨምሮ ተቋርጧል።

(ዛሬ ከ #ኢሰመኮ የተላከል ሙሉ መግለጫ በዚህ ታገኛላችሁ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/82609?single)

@tikvahethiopia
#ሺርካ

✦ " 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት (አያት ፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ ፣ የ39 ቀን ጨቅላ) ጨምሮ 17 ስዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል " - የቲክቫህ ቤተሰብ አባል

✦ " ከሟቾቹ ውስጥ ከ70 ዓመት አዛውንት እስከ 26 ቀን ህጻን ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል " - ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ (ለቪኦኤ)

✦ " ጥቃቱን ያደረሰው አሸባሪው ሸኔ ነው " - የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን (ለቪኦኤ)

✦ " እኛ ንፁሃን ላይ ጥቃት አላደረስንም " - የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ለቪኦኤ)

✦ " ባለሞያ መድበን ምርመራ ጀምረናል " -
ኢሰመኮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ፤ ሺርካ ወረዳ ፤ በተፈጸመ ጥቃት ንጹሐን ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መሞታቸውን እና የዐይን እማኞችና መልክታቸውን ያደረሱ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

አንድ #የአካባቢው ነዋሪ የቤተሰባችን አባል በላኩልን መልዕክት ፤ " ህዳር 13 /2016 በግምት ከምሽቱ 2:30 አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ እና በታጠቁ ኢ - መደበኛ ሀይሎች በሽርካ ወረዳ ሶሌ ዲገሉ ጉና እና ጢጆ ለቡ በተባሉ የገጠር ቀበሌዎች በተፈፀመ ጥቃት 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት (አያት ፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ ፣ የ 39 ቀን ጨቅላ) ጨምሮ 17 ስዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ በተመሳሳይ ሰዓት በተፈፀመ በሌላኛው ጥቃት ደግሞ 11 በድምሩ 28 ሰው ሲልፍ ሁለት ህፃናት ደግሞ ቆስለው ህክምና ላይ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

ቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት ክፍል በጉዳዩ ላይ በሰራው ዘገባ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ሦስት ቀበሌዎች ሐሙስ ህዳር 13 እና ሰኞ ህዳር 17 ቀን በተፈጸመ ጥቃት #36_ሰዎች መሞታቸውን ገልጿል።

ከሟቾቹ ገሚሶቹ የሁለት ቤተሰብ አባላት መሆናቸውን በዘገባው ጠቅሷል።

ቃላቸውን የሰጡ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ ነዋሪ ፤ " ህዳር 13 ለ 14 አጥቢያ ለቡ በተባለው ቀበሌ ላይ 11 ሰው አንድ ላይ ሰብስበው እነዚህ ታጣቂዎች አንድ ላይ ረሽነዋል። ሶሌ ዲገሉ በተባለው ቀበሌ ደሞ 17 ሰው አስሩ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው ሰብስበው ረሽነዋል። እነዚህ 17ዱ በአንድ ጉድጓድ 11ቱ በአንድ ጉድጓድ ተቀብረዋል። የዚህን ሀዘን ሳንጨርስ እንደገና በሦስተኛው ቀን ለቡ በተባለው ቀበሌ የአንድ ቤተሰብ አባላት 8 ሰዎች ረሽነዋል። እነዚህም በአንድ ጉድጓድ ተቀብረዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ነዋሪው አክለው፤ " ከእነዚህ ከሟቾቹ ውስጥ ከ70 ዓመት አዛውንት እስከ 26 ቀን ህጻን ነፍሰጡር  እናቶች ይገኙበታል" ያሉ ሲሆን " የሦስቱ ቦታ ጥቃቶች በተመሳይ መልኩ ቤት እየገቡ አንድ ቦታ ያሉ ሰዎችን መረሸን ነው። ህጻን የለም አዋቂ የለም ገብተው መረሸን ነው። የአማርኛ ስም ያላቸው፣ የአማራ ስም ያላቸውና የኦርቶዶክስ እምነት አማኝ ላይ ያተኮረ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ጥቃቱን ማን እንደፈጸመ የተጠየቁት ነዋሪው " ምንም የሚታወቅ ነገር የለም የታጠቁ ኃይሎች ናቸው እከሌ ልንላቸው አንችልም። " ሲሉ ምላሻቸውን ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሓላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ፣ ለጥቃቱ መንግሥት ' ሸኔ ' እያለ ከሚጠራው (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ታጣቂ ቡድን) ተጠያቂ አድርገዋል።

ኃላፊው ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ " በሽርካ ወረዳ ሶሌ ዲገሉ፤ ጢጆ ለቡ፤ ሲላ ዋጂ አሸባሪው ሸኔ ንጹሐን ላይ ጥቃት ፈጽሟል። ከ2 ዓመት ህጻንን እስከ አቅመ ደካማ ሴቶችን ላይ አነጣጥሮ እኔ ባለኝ መረጃ የ27 ሰዎች ህይወት አልፏል " ብለዋል።

አክለውም " ይኼ አሸባሪ ቡድን ባሳለፍነው ሳምንት ቡኖ በደሌ ጨዋቃ ወረዳ ላይ በኢትዮጵያ የጸጥታ አካል በተወሰደበት እርምጃ ብዙ ኃይሉ ሙትና ቁስለጫ በመሆኑ ይሄንን ለመበቀል ብሎ በአርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ይሄንን ጥቃት ፈጽሟል።" ሲሉ ከሰዋል።

በመንግሥት " ኦነግ ሸኔ " የተባለውና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል ቃል አቀባይ የሆኑት ኦዳ ታርቢ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ክፍል በሰጡት ምላሽ ውንጀላውን #አስተባብለዋል፡፡

" እኛ ኃይላችን በተባለው አከባቢ #በሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው እርምጃ፤ ያጠፋው የሰላማዊ ሰዎች ህይወትም የለም። ከህዳር 14 - 17 ድረስ በሥርዓቱ ኃይል ብዙ ሰው ተገሏል፤ ብዙ ቤትም ተቃጥሏል። ይህም በምስራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ነው የተፈጸመው አዛውንቶችም ተገለዋል። ይህንን ለማድበስበስ ነው ጣታቸውን በእኛ ላይ የሚጠቁሙት " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሓላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ግን ይህ ኃይል የሚፈጸጸምማቸውን ጥቃት መካድ ባህሪው ነው ሲሉ ገልጸውታል።

አስተያየታቸውን የሰጡን የቲክቫህ ቤተሰቦች ፤ " እዚሁ ወረዳ ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ ግድያ እንደነበረ ቢታወቅም በአካባቢው ያሉ የመንግስት ታጣቂዎች ለጉዳዩ የሰጡት ትኩረት አነስተኛ ስለነበር ይህ ሁሉ ሰው ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጭፈዋል። የአካባቢው ህዝብም በአካባቢው ለመኖር ዋስትና ስለሌለው አካባቢውን ለቆ ለስደት እየተዳረገ ነው፡፡" ሲሉ ተናግረዋል።

በኦሮሚያ ክልል ፤ ምሥራቅ አርሲ ዞን ፤ ሽርካ ደረሰ ስለተባለው ጥቃት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን የኮሚሽኑ የክትትልና ምርመራ ስራ ክፍል ሲኒየር ዳይሬክተር ሚዛኔ አባተ (ዶ/ር)፣ " መረጃ ደርሶናል እያየነው ነው " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

" አሁን ላይ በዝርዝር የምናገረው ነገር የለም። ነገር ግን እኛ ጉዳዮች እንደዚህ በሚደርሱን ሰዓት ጉዳዩን የሚከታተል ባለሙያ እንመድባለን፣ በዚህም ምርመራ እናደርጋለን። ያ ነገር የተጀመረ መሆኑን ነው መናገር የምችለው " ሲሉ ገልጸውልናል።

@tikvahethiopia
#ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፦

#አማራክልል

በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አምበላ ቀበሌ በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ቀናት በተፈጠረው ብሔር ተኮር ግጭት ሞት እና የአካል ጉዳት እንዲሁም በኢንቨስትመንት ቦታዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።

በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፣ ፈጣም ሰንቶም እና በቆጣቦ ቀበሌዎች ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. እና በኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. " ኢመደበኛ " የአማራ ታጣቂዎች መሆናቸው የተገለጸ ቡድኖች በሰነዘሩት ብሔር ተኮር ጥቃት እና ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ደርሷል።

በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ነዋሪዎች ተፈናቅለው በቡሬ ዙሪያ ወረዳ በሚገኙ አጎራባች ቀበሌዎች እና ወደ ኦሮሚያ ክልል ለመሄድ ተገደዋል። የቀንድ ከብቶች ተዘርፈዋል።

#ቤኒሻንጉልጉሙዝ

አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ ሥር በሚገኙ ቤልሚሊ፣ አልከሻፊ እና ቤላደሩ ቀበሌዎች በሚኖሩ የቤኒሻንጉል ብሔር ተወላጆች እና አብረው በሚኖሩት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ላይ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ-ሸኔ) ታጣቂ ቡድን አባላት በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

በጥቃቱ 17 ሰዎች መገደላቸው ፣ አንድ ሽማግሌ ታፍነው መወሰዳቸው፣ በ7 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።

በሦስቱ ቀበሌዎች ያሉ መንደሮች በአብዛኛው የተቃጠሉና የወደሙ መሆኑን፣ የእርሻ ሰብልና የቤት እንስሳትን ጨምሮ የንብረት ውድመት ደርሷል።

የቀበሌዎቹ ነዋሪዎች ጥቃቱን በመሸሽ ወደ አጎራባች ቀበሌዎችና በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው መነሲቡ ወረዳ (ኦሮሚያ ክልል) ተፈናቅለዋል።

#ኦሮሚያክልል

- በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ ኅዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም. በጢጆ ለቡ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በኋላ ማንነታቸው በውል ያልተለየ ታጣቂዎች በፈጸሙት ብሔር/ማንነት ተኮር ጥቃት 7 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና 3 ጎረቤቶቻቸው ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለዋል።

በዚያው ዕለት ታጣቂዎቹ በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ቢያንስ 12 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል።

በሶሌ ዲገሉ ቀበሌ ከተገደሉ 12 ሰዎች መካከል አሥራ አንዱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።

በኅዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም. በወረዳው በኮኘ ቀበሌ ታጣቂዎቹ በፈጸሙት ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የነበሩ 8 ሰዎችን ገድለዋል።

ጥቃት አድራሾች ሟቾችን ከቤት እያስወጡ #አሰልፈው_እንደገደሏቸው፣ የተወሰኑትም በቤታቸው ውስጥ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

ከሟቾች መካከል #ጨቅላ_ሕፃንን ጨምሮ ነፍሰጡር ሴቶች እና ከ80 ዓመት በላይ የሆናቸው አረጋዊ ይገኙበታል፡፡

ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሳቸው መሆኑን ለኮሚሽኑ ገልጸው፤ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል፡፡

በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፣ የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን አባላት የነበሩት 9 ምዕመናን፣ ሽማግሌዎች፣ የወጣቶች ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ሌሎች አገልጋዮችን ኅዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊት 8፡00 ሰዓት አካባቢ እስካሁን ማንነታቸው ባልተለዩ በታጠቁ ቡድኖች ተገድለዋል።

ግድያው የተፈፀመድ መላኮ መናሞ ቀበሌ ባለው ጫካ ውስጥ ሲሆን ገዳዮችን  አስክሬናቸውን መጣላቸው ለማረጋገጥ ተችሏል።

(የኢሰመኮ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#Amhara #Merawi

በአማራ ክልል ፤ በየጊዜው በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መከላከያ እና በ " ፋኖ " ታጣቂ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ይደረጋሉ።

በእነዚህ ግጭቶችም በሁለቱም በኩል ከሚሞተው የግጭቱ ተካፋይ ባለፈ ንፁሃን ሰዎች ሰለባ እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተገልጿል።

ምንም እንኳን #መንግሥት ፤ " ከእውነታው ያፈነገጠ እና ሚዛናዊነት የጎደለው " ብሎ ቢያጣጥለውም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮኒሽን  (#ኢሰመኮ) ይፋ አድርጎት በነበረው ሪፖርት በክልሉ ፦

- የአንድ ዓመት ከሰባት ወር #ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች በድሮን መገደላቸው / የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው።

- በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት #ሲቪል_ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ።

- በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት #ከሕግ_ውጪ የሆኑ ግድያዎች እንደሚፈፀሙ።

- ከዚህ ቀደም ግጭቶች በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦
" ፋኖን ትደግፋላችሁ "
" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "
" መሣሪያ አምጡ "

" የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ በርካታ #ግድያዎች መፈጸማቸውን በይፋ ማሳወቁ አይዘነጋም።

ከሰሞኑን ዳግሞ በሰሜን ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል፣ ሰኞ ጥር 20/2016 ዓ/ም የነበረውን ውጊያ ተከትሎ በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።

አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ገለጻ ፤ በሰሞኑ ተኩስ እሳቸው የሚያውቋቸው ብቻ 15 ወጣቶች መገደላቸውን ተናግረዋል።

ከዚህም ባለፈ ግን ፤ " የሟቾቹን ቁጥር በዚህ ወቅት ለመግለጽ መሞከር የጥቃቱን አድማስ ያሳንዋል እንጂ አይገለጸውም" ብለዋል።

እኚሁ ነዋሪ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ሰዎችን ቁጥር በሂደት እንጂ አሁን ሁሉንም ማወቅ እንደማይቻል ገልጸው ፤ " የዚህ ህዝብ ጭፋጨፋ ግን መቼ ነው የሚያበቃው? " ሲሉ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ የሆስፒታል ሰዎችና የአይን እማኞች በከተማው ከ50 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።

አብዛኞቹ ነዋሪዎች ግድያው የተፈጸመው በቤታቸው እና በመንገድ ላይ በተገኙ ሰላማዊ ሰዎች ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

አንድ የህክምና ባለሙያ 13ት ሰዎች ከአስፓልት ዳር መገደላቸውን እንደሚያውቁ ተናግረው በአጠቃላይ በከተማዋ በዚያ ዕለት 85 ሰዎች መገደላቸውን አመልክተዋል።

አንድ የአይን እማኝ በርካታ ቀብሮች ላይ መገኘታቸውን ጠቅሰው የሟቾችን ቁጥር " ከ100 በላይ ነው " ብለዋል። ጥቃቱ በተፈጸመ ማግስት ጠዋት ላይ 48 አስከሬን መቆጠራቸውን ተናግረው ፤ " ከማርዘነብ ሆቴል እስከ በረድ ወንዝ ድረስ ግራ እና ቀኝ አስከሬን ብቻ ነበር " ብለዋል።

የሟቾችን ቁጥር 115 ገደማ የሚያደርሱ አንድ የዐይን እማኝ ደግሞ መከላከያ ከተማዋን ከተቆጣጠረ በኋላ ስታዲየም እና ጤና ጣቢያ በተባሉ ሰፈሮች " ከ6 ዓመት ህጻን እስከ 75 ዓመት አዛውንት " ድረስ ግድያ ተፈጽሟል ብለዋል።

የሆስፒታል ሠራተኛ የሆኑት የዐይን እማኝ በከተማዋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 25 ሰዎች ቆስለው መጥተው " የተረፈ የለም " ሲሉ ገልጸዋል።

" 24ቱ ሆስፒታል የመጡት ሞተው ነው። አንዲት የ6 ወር ነፍሰ ጡር ሴት ከነ ነፍሷ መጥታ ሆስፒታል እንደደረሰች አርፋለች። አጠቃላይ 25 ነበር የመጡት " ብለዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ #በመርዓዊ_አስተዳደር ህንጻ ውስጥ በነበሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፋኖ ታጣቂዎች ሰኞ ጠዋት ድንገተኛ ጥቃት ፈፀመው እንደነበርና ለዚህ ምላሽ " የበቀል እርምጃ " በመወሰዱ ነው ለበርካታ ሰዎች ግድያ ምክንያት የሆነው ብለዋል።

ስለ ግድያው ምን ምላሽ እንዳለቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የአማራ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ  መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፣ " ስብሰባ ላይ ነኝ መልሸ ልደውል " ብለዋል።

መንገሻ (ዶ/ር) ይህን ያሉት እንዲያብራሩ የተፈለገውን ጥያቄ በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ሲሆን፣ በድጋሚም ስልክ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

እንዲሁም፣ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና በኮሚዩኒኬሽን በኩል ያለውን የመርዓዊ ጉዳይ ማብራሪያ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ " የሚል የፅሑፍ መልዕክት (SMS) ቢላክላቸውም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።

በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ምክትል፣
* የክልሉና የሰሜን ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት፣
* የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ስለጉዳዩ ምን ምላሽ እንዳለቸው ለማወቅ እና ሃሳባቸውን ለማካተት ስልክ ቢደውልም ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፤ " መረጃው ደርሶናል (የመርዓዊ ጉዳይ) ። እያረጋገጥን ነው " ብለዋል።

አክለው ፣ "የጸጥታ ጉዳይ ስለሆነ ትንሽ መንቀሳቀስና መረጃ መሰብሰብ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል ሊዘገይ ይችላል። ግን እያጣራን ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara #Merawi በአማራ ክልል ፤ በየጊዜው በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መከላከያ እና በ " ፋኖ " ታጣቂ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ይደረጋሉ። በእነዚህ ግጭቶችም በሁለቱም በኩል ከሚሞተው የግጭቱ ተካፋይ ባለፈ ንፁሃን ሰዎች ሰለባ እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ምንም እንኳን #መንግሥት ፤ " ከእውነታው ያፈነገጠ እና ሚዛናዊነት የጎደለው " ብሎ ቢያጣጥለውም የኢትዮጵያ…
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአማራ ከልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በ20/05/2016 ዓ.ም በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች መካከል በነበረ ግጭት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሱት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

በእዚህ ግጭት ምክንያት በመርዓዊ ከተማ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ እንደነበር ፤ በግጭቱ ተሳትፎ የሌላቸው ሰዎች ላይ ግድያ፣ የአካል ጉዳት፣ ድበደባ፣ ማስፈራራትና ሌሎችም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈፀማቸውን ገልጿል።

በአካባቢው በነበረው ግጭት ምክንያት ከ80 በላይ የሆኑ በግጭቱ ተሳትፎ የሌላቸው ሰዎች የተገደሉ መሆኑን ከእነዚህም መካከል ሁለት ሴቶች እንደሚገኙበትና ለግድያው ምክንያት የነበረው በግጭቱ ወቅት የነበረው ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር አመልክቷል።

በተጨማሪም ቤት ለቤት በመዘዋወር ግድያ መፈጸሙን ከአካባቢው ካሰባሰብኳቸው መረጃዎች ለመረዳት ችያለሁ ብሏል።

በእዚህ ግጭት ወቅት አካል ጉዳተኞች ላይ ድብደባ የተፈጸመ መሆኑንና ከተገደሉ ሰዎች መካከል አንድ የ17 አመት ታዳጊ እንደሚገኝበት ከአካባቢ ከነበሩ የአይን እማኞች ለመረዳት እንደተቻለ ገልጿል።

ከአይን እማኞች አገኘሁት ባለው መረጃ መሰረት ፦
- ወንዶችን ቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ ወደመንገድ በማውጣት የጅምላ ግድያ መፈጸሙን፤
- ከ21/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሟቾች አስከሬን በመርዓዊ ከተማ ማሪያም ቤተክርስቲያን በጅምላ እየተቀበሩ የነበረ መሆኑን፤
- በከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ምክንያት የአካባቢው ነዋሪ አካባቢውን ለቆ እየወጣ መሆኑን አመልክቷል።

ኢሰመጉ ከላይ የተዘረዘሩትን ጉዳዮች በአካል በመገኘት ምርመራ በማድረግ ለማረጋገጥ እንዳልቻለ በመግለጫው አሳውቋል።

ይህንን ጉዳይ አስመልከቶ የአካባቢው የጸጥታው ሁኔታ ሲፈቅድ ተጨማሪ የምርመራ ስራን በማከናወን ዝርዝር መግለጫን እንደሚያዘጋጅ ይፋ አድርጓል።

እስካሁን በመንግስት በኩል የተሰጠ ምላሽም ይሁን መረጃ የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቀናት በፊት በመርዓዊ ጉዳይ ባዘጋጀው አንድ ዘገባ  ፦
* የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ምክትል፣
* የክልሉና የሰሜን ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት፣
* የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ስለጉዳዩ ምን ምላሽ እንዳለቸው ለማወቅ እና ሃሳባቸውን ለማካተት ስልክ ቢደውልም ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሀሳባቸውን ለማካተት ሳይችል ቀርቷል።

በክልሉ ኮሚኒኬሽን በኩል ምላሽ ለማግኘት ለአንድ ኃላፊ ስልክ ብንደውልም ጥያቄውን በዝርዝር ከሰሙ በኋላ " ስብሰባ ላይ ነኝ መልሼ ደውላለሁ " ቢሉም አልደወሉም ፤ በድጋሚም ስልክ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

" እባክዎ ስልክዎን ያንሱና በኮሚዩኒኬሽን በኩል ያለውን የመርዓዊ ጉዳይ ማብራሪያ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ " የሚል የፅሑፍ መልዕክት (SMS) ቢላክላቸውም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " መረጃው ደርሶናል (የመርዓዊ ጉዳይ) ። እያረጋገጥን ነው " ብለዋል።

አክለው ፣ " የጸጥታ ጉዳይ ስለሆነ ትንሽ መንቀሳቀስና መረጃ መሰብሰብ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል ሊዘገይ ይችላል። ግን እያጣራን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#StateofEmergency #EHRC

" በእስር የቆዩ ሰዎች ሊለቀቁ ይገባል " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (#ኢሰመኮ) ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አተገባበር ጋር በተያያዘ በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠየቀ።

በአማራ ክልል በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች (በተለምዶ “#ፋኖ”) መካከል ከሚካሄደው የትጥቅ ግጭት ጋር ተያይዞ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው እና ጥር 24 ቀን 2016 ዓ/ም ለተጨማሪ 4 ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ ተፈጻሚነት አብቅቷል።

ይህንን ተከትሎ በእስር የቆዩ ሰዎችን የመልቀቅ ሂደት እንዲቀጥል ኢሰመኮ አሳስቧል።

ኮሚሽኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈጻጸም በሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ያለውን ተጽዕኖ በተመለከተ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

ከአዋጁ ትግበራ ጋር የተስተዋሉ ክፍተቶችንና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያመላክቱ፣ እንዲሁም ምክረ ሐሳቦችን ያካተቱ ግንቦት 20 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ያደረገውን ጋዜጣዊ መግለጫ ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት በርካታ የክትትልና የምርመራ ሪፖርቶች ይፋ ሲያደርግ የቆየ መሆኑ አስታውሷል።

በዚሁ አዋጅ አተገባበር ዐውድ ውቅጥ #በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ማድረግን ጨምሮ ወደ መደበኛው የሕግ አተገባበር ሂደት መመለስ፣ እንዲሁም በተለያዩ የክልል አካባቢዎች የተጣሉ የእንቅስቃሴ ገደቦች እንዲነሱ እና ሌሎችም ማኅበረሰባዊ #አገልግሎቶች እንዲመለሱ ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል።

#EHRC #Ethiopia #StateofEmergency

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ_ዓመታዊ_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2015_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ_ወር_2016_ዓ.pdf
7.8 MB
#ኢሰመኮ : የትጥቅ ግጭቶች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋነኛ ምክንያት ሆነው መቀጠላቸውን ኢሰመኮ አሳውቋል።

ይህም  " አካታችና ተዓማኒ የሆነ ሰላማዊ መፍትሔ እና የሽግግር ፍትሕ ሂደት አፋጣኝ አስፈላጊነት አመላካች ነው "
ብሏል።

ይህን ያለው ዛሬ ይፋ ባደረገው 3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ ነው።

ሪፖርቱ ባለ 132 ገጽ ሲሆን ከሰኔ ወር 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ/ም ያለውን ጊዜ ይሸፍናል።

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia