TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የአሜሪካ ኤምባሲ⬇️

ረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2011 ዓ.ም. ‹‹በአዲስ አበባ ከተማ ታላቅ ሕዝባዊ ሠልፍ እንደሚኖር ተገምቷል፤›› ብሎ የኤምባሲው ሠራተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ፣ በተጠቀሰው ቀንም ኤምባሲው ሥራ እንደማይኖረው ገልጾ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣው ማሳሰቢያ በርካቶችን ግር አሰኝቷል፡፡ ኤምባሲው ከአስተማማኝ መረጃ አረጋግጫለሁ ያለለት ሠልፍም #አልተካሄደም፡፡

ኤምባሲው በድረ ገጹ ሁሉም የቪዛ አገልግቶችና የአሜሪካ ዜጎች አገልግሎት ቀጠሮዎች ሙሉ በሙሉ መሰረዛቸውንና አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች በድረ ገጹ አማካይነት ሌላ ቀጠሮ እንዲይዙ ገልጿል፡፡ የኢሚግሬሽን ቪዛ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ሌላ ቀጠሮ ተዘጋጅቶ እንደሚጠሩና ከዚህ ውጪ ያሉ የቪዛ አገልግሎት የሚጠይቁ ሰዎች በኤምባሲው ድረ ገጽ ቀጠሮ እንዲያሲዙ አሳስቦ ነበር፡፡

ኤምባሲው ይህን ካለ በኋላ በሠልፉ የሚሳተፉ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ መንገድ መልዕክታቸውን እንዲገልጹ እንደሚያበረታታም አስታውቋል፡፡

ይሁን እንጂ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣውን መግለጫ ያየው የእንግሊዝ ኤምባሲ፣ ‹‹የአሜሪካ ኤምባሲና የኢንተርናሽናል ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የእግሊዝ ኤምባሲ ሌላ ማሳሰቢያ እስካልወጣ ድረስ መደበኛ ሥራውን ያከናውናል፤›› ሲል በትዊተር ገጹ ላይ አስታውቋል፡፡ የኤምባሲው መረጃ የደረሳቸው ዓለም አቀፍ ተቋማትም ሠራተኞቻቸው ሥራ እንዳይገቡ ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች ከኤምባሲው ጋር ግንኙነት ያላቸው የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞችም በተመሳሳይ ሥራ እንዳልገቡ ሪፖርተር ማረጋገጥ ችሏል፡፡

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ቃል አቀባይ ኒክ ባርኔት ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ፣ በተጠቀሰው ቀን ሠልፍ እንደሚኖር አስተማማኝ መረጃ እንደደረሳቸውና በዚህ መረጃ መሠረት ኤምባሲው እንደወሰነ ገልጸው፣ ይኼንን ዓይነት ውሳኔ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ኤምባሲው #በሕግ ስለሚገደድ በይፋ እንዳጋራው ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን ሰዎች ኤምባሲው #ድብቅ አጀንዳ እንዳለው አድርገው እንደተመለከቷቸውና ይህ ማሳሰቢያ የዜጎችን ደኅንነት ከማስጠበቅ የዘለለ ሌላ ሚና እንደሌለው ተናግረዋል፡፡

‹‹ሠልፉ #ሰላማዊ ቢሆን እንኳን ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል፡፡ ሰዎች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ላይችሉና በቤታቸውና በመሥሪያ ቤታቸው መካከል ሆነው መንቀሳቀስ ሊሳናቸው ይችላል፡፡ እኛም አገልግሎቶችን ለመስጠት እንቸገራለን፤›› ሲሉ ባርኔት አስታውቀዋል፡፡ ስለዚህ አስተማማኙ ውሳኔ ሠራተኞቻችን ቤት እንዲቆዩ መምከር ነው ብለዋል፡፡

ይሁንና በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት ሠልፍ በሌለበት ጊዜ ኤምባሲው ይኼንን መግለጫ በማውጣቱ በርካቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲተቹና የሐሰት መረጃ አሠራጭ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

ይሁን እንጂ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ ለረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2010 ዓ.ም. የተጠራ ምንም ዓይነት ሠልፍ አለመኖሩን አስታውቋል። መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት በአዲስ አበባ የተጠራ ሠልፍ አለ በማለት ያወጡት መረጃ ሙሉ በሙሉ #የተሳሳተም ነው ብሏል።

©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥረት‼️

• በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ሲከስር ነበር፡፡

• የባንክ ዕዳውም 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡

በቀድሞው ኢህዴን (አዴፓ) በዘላቂ በጎ አድራጎት ወይም ኢንዶውመንት ቁመና ይዞ የተመሠረተው ጥረት ኮርፖሬት 20 ኩባንያዎች አሉት። ከእነዚህ ውስጥ ከሰባቱ በየዓመቱ 100 ሚሊየን ብር አካባቢ ይከስራል።

የጥረት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አምላኩ አስረስ እንደሚሉት በቀደመው አመራር ጥረት 11 ቢሊዮን ብር ጥሬ ሀብት አለው ተብሎ ሪፖርት የተደረገውም ስህተት ነው። የጥረት በአሁኑ ወቅት ያለው ጥሬ ሀብት 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ሲሆን 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን አካባቢ የባንክ ዕዳ አለበት። ከዚህም በተጨማሪ ካሉት 20 ኩባንያዎች በሰባት ኩባንያዎች በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ይከስራል።

ጥረት በትራንስፖርት ዘርፉ የተሠማሩ 500 ተሽከርካሪዎች አሉት እየተባለ ሪፖርት ሲደረግ ቢቆይም በተግባር ያሉት ተሸከርካሪዎች ግን 348 ናቸው። ከዚህ ውስጥ 48ቱ ብቻ ዓመት እስከ ዓመት ይሠራሉ፤ ሌሎቹ የተበላሹ ናቸው። ጥረት ከኪሳራው ለመውጣት አዲስ ፍኖተ ካርታ እያዘጋጀ ሲሆን የመዋቅር እና የአመራር ለውጥም እያደረገ እንደሆነ ዶክተር አምላኩ አስረድተዋል። አጥፊዎችም #በሕግ የሚጠየቁ ይሆናል ብለዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢሶዲፓ🔝ኢህአዴግ በሕገወጥነትና በአምባገነናዊነት ያዋቀራቸው የመስተዳደር #አከላለሎች ዛሬ ለተፈጠረው የመለያየት ስሜት እና ግጭቶች ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ሲሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ከሰሰ፡፡ መንግሥት ለዚህ ችግር አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚፈልግም አሳስቧል፡፡ ሕዝቡ በበኩሉ ለተፈጠሩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ #በትግስትና #በሕግ አግባብ እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል፡፡

©VOA የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ታዬ ከሰሞኑን ምን ሲሉ ነበር ? ዛሬ ታህሳስ 1/2016 ዓ/ም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፊርማ ባረፈበት ደብዳቤ ከሰላም ሚኒስትር ዴኤታነት መነሳታቸው የተገለፀላቸው አቶ ታዬ ደንደአ ከሰሞኑን አነጋጋሪ ቃለ ምልልሶችን ሲሰጡ ነበር። ለአብነት ፦ ▪️የቲክቫህ - ኢትዮጵያ የቤተሰብ አባልን ጨምሮ ፤ ለተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች በአዳማ በነበረ አንድ ፕሮግራም በሰጡት ቃለ ምልልስ ተከታዮቹን…
አቶ ታዬ #በሕግ የሚያስጠይቃቸው ጉዳይ ይኖር ይሆን ?

" በሕግ መጠየቅ ምን ችግር አለው፤ ነገር ግን ሕግ የታለና በሕግ ይጠይቁኛል። ከጠየቁኝ ደግሞ ዝግጁ ነኝ " - አቶ ታዬ ደንደአ

አቶ ታዬ ደንደአ ከሰላም ሚኒስትር ዴኤታነት መነሳታቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ከደረሳቸው እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ጠንካራ ትችት ከሰነዘሩ በኃላ ማምሻውን ለ " ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ " ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

አቶ ታዬ ደንደአ በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከሥልጣን የተሰናበቱት በአገሪቱ ያለው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ በማቅረባቸው እንጂ ሌላ ምክንያት እንደሌለ ተናግረዋል።

" ስለእርቅ ስለተናገርኩ ጦርነት ይቁም ስላልኩ እንጂ ሌላ ምክንያት የለም " ያሉት አቶ ታዬ፣ " በጦርነቱ ጊዜ ጦርነቱን ስደግፍ፣ ሲያበረታቱኝ ነበር። ሕዝቡ ይታረቅ ስንል ነው ያመማቸው። ጠርተው አላናገሩኝም። በአካል አልተገናኘንም " ሲሉ ተናግረዋል።

ስንብታቸውን በተመለከተ #በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ያሰፈሩትን ጠንካራ ቃላትን የተጠቀሙት ትችትን በተመለከተ የተጠየቁት አቶ ታዬ ደንደአ ፤ " ይሄ እውነት ነው። ለሰው አያዝኑም። የሰው ልጅ ሞቶ አውሬ እየበላው ስለ ፓርክ ያወራሉ። ሰው የሚበላው አጥቶ እየሞተ በብዙ ገንዘብ ቤተ መንግሥት ያስገነባሉ " በማለት ወቅሰዋል።

በማህበራዊ ገፃቸው በፃፉት ትችት በሕግ ሊያስጠይቃቸው የሚችል ነገር ይኖር እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ታዬ ለዚህ ዝግጁ መሆናቸውን ፤ ነገር ግን ይህ የሚሆንበት ዕድል እንደሌለ ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል።

" በሕግ መጠየቅ ምን ችግር አለው ታዲያ። ነገር ግን ሕግ የታለና በሕግ ይጠይቁኛል። ከጠየቁኝ ደግሞ ዝግጁ ነኝ። " ብለዋል።

የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን ሆነው በጠንካራ ትችታቸው የሚታወቁት አቶ ታዬ ሰሞኑን በተከታታይ የሰነዘሯቸው አስተያያቶች ለስንብታቸው ምክንያት ይሆናል ብለው እንደማያምኑም ተናግረዋል።

አቶ ታዬ ፤ " ከዚህ ጋር የሚገናኝ አይመስለኝም። ከፓርቲያችን መርሆች ውስጥ ነጻነት አንዱ ነው። ከዚህ መርህ በተቃራኒ መቆም ተገቢ አይደለም። እኔ ስናገር የነበረው ይህንን መርህ መሠረት በማድረግ ነው " ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ሆነ ሰላም ሚኒስቴር እስካሁን ስለጉዳዩ ያሉት ነገር የለም። ነገር ግን አቶ ታዬ ከስልጣን መሰናበታቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TayeDendea

አቶ ታዬ ደንደአ ትላንት በይፋዊ ፌስቡክ ገፃቸው ከስልጣን መነሳታቸውን የሚገልፅ የስንብት ደብዳቤ አያይዘው ከለጠፉ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ጠንካራ ቃላትን ተጠቅመው ትችት ከሰነዘሩ በኃላ #በሕግ_ሊያስጠይቃቸው የሚችል ጉዳይ ይኖር እንደሆነ ተጠይቀው ነበር።

አቶ ታዬ ፤ " በሕግ መጠየቅ ምን ችግር አለው ፣ ነገር ግን ሕግ የታለና በሕግ ይጠይቁኛል። ከጠየቁኝ ደግሞ ዝግጁ ነኝ " የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።

በሕግ ሊጠየቁ የሚችልበት እድልም እንደሌለ ተናግረው ነበር።

ዛሬ የፀጥታ እና የደህንነት የጋራ ግብረኃይል አቶ ታዬን ደንደአን በሕግ ቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሲሆን መኖሪያ ቤታቸው ላይም ብርበራ አድርጓል።

ግብረ ኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአን ፦

- በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ሲፈፀሙ በነበሩ የሽብር ተግባራት በተለይም ደግሞ #ከእገታ ጋር በተያያዘ እጃቸው እንዳለበት አሳውቋል።

(አቶ ታዬ ደንደአ በ #ሰላም_ሚኒስቴር ውስጥ ሆነው በተለያዩ ጊዜ በሚፈፀሙ የእግታ ጉዳዮች እጃቸው እንዳለበት የታወቀው መቼ ነው ? ከዚህ ቀደም ታውቆ ከሆነ ለምን እስከዛሬ ዝም ተባሉ ለሚለው ጉዳይ የተብራራ ነገር የለም)

- የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰላምን ለማስፈን ከመስራት ይልቅ ከፀረሠላም ኃይሎች ጋር ተሳስረው ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ ነበር ብሏቸዋል።

- መንግስት እና የፓርቲ መዋቅሩን በሴራ ለመናድ በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ ነበር ብሏቸዋል።

- መንግሥት በሽብርተኝነት ከፈረጀው ከኦነግ ሸኔ አመራሮች እና በሽብር ወንጀል ከሚጠረጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ትስስር ፈጥረው መንግስትን በአመፅ፣ በሽብርና በትጥቅ ለመጣል ሲያሴሩ ተደርሶባቸዋል ብሏል።

አቶ ታዬ ደንደአ ከሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን እና በራሳቸው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የተለያዩ አስተያየቶችን ሲሰጡ የነበረ ሲሆን ትላንት ታሕሳስ 1 በኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተፃፈ ደብዳቤ ከስልጣን እንዲነሱ ተደርገዋል።

አቶ ታዬ ከስልጣን ለመነሳታቸው ምክንያቱ ጦርነት ተቃውመው ስለእርቅ ስለተናገሩ እንጂ ሌላ ምክንያት እንደሌለ ተናግረዋል። " በጦርነቱ ጊዜ ጦርነቱን ስደግፍ ሲያበረታቱኝ ነበር ሕዝቡ ይታረቅ ስንል ነው ያመማቸው " ያሉት አቶ ታዬ ሰላምን በመደገፌ ነው ከስልጣን የተነሳሁት ብለዋል።

ግብረ ኃይሉ ግን አቶ ታዬ ስልጣን ላይ ቁጭ ብለው እራሳቸው ያሉበትን #መንግስት እና #ፓርቲ ለመናድ መንግስትንም በሽብር ትጥቅ ለመጣል ከፀረሠላም ኃይሎች ጋር ሲሰሩ እንደደረሰባቸው አመልክቷል።

ልክ በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ሲያውቁ ደግሞ #ታጋይ ለመምሰል በየማህበራዊ ትስስር ገፆች ፀረ-ሰላም ፅሁፎችን እና ንግግሮችን ሲያስተላልፉ ነበር ብሏል።

@tikvahethiopia