TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሱማሌ ክልል‼️

በቱሊ ጉሌድ ወረዳ መስተዳደር በጌሪና በጃርሶ ጎሳዎች መካከል የተነሳ #ግጭት ለሰው ህይወት ህልፈትና ለአካል ጉዳት መንስኤ እየሆነ ይገኛል፡፡

በሶማሊ ክልል መስተዳድር በፋፈን ዞን የቱሊ ጉሌድ ወረዳ ውስጥ በሚኖሩት የጌሪና የጃርሶ ጎሳዎች መካከል በትላንትናው እለት ዳግም ባገረሸ ግጭት ለሰው ህይወት ህልፈትና በርካቶችን ለአካል ጉዳት ዳርጓል፡፡

በዚሁ ግጭት ሳቢያ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ ቁስለኞች በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና በሆነችው ጅግጅጋ ከተማ የካራመራ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ለመስማት ተችሏል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በቱሉ ጉሌድ ወረዳ ውስጥ በሚኖሩት የጌሪና የጃርሶ ጎሳዎች መካከል ለብዙ ጊዜ እልባት ሳያገኙ የቆዩ #አለመግባባቶች የነበሩ ሲሆን እነዚሁ አለመግባባቶች #ዘላቂ የሆነ #መፍትሄ ባለማግኘታቸው በሁለቱ ጎሳዎች መካከል ዳግም ግጭት እንዲያገረሽና ለሰው ህይወት ህልፈትና ለአካል ጉዳት የዳረገ መንስኤ ሊሆን ችሏል፡፡

የሶማሊ ክልል አስተዳደር በሁለቱ ጎሳዎች መካከል ላሉት አለመግባባቶች ዘላቂ የሆነ መፍትሄ በመስጠት ይኖርበታል።

©rajo
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አባ ገዳዎች🕊

"በሀገሪቱ #ዘላቂ_ሰላም እንዲሰፍን #የበኩላችን_አስተዋጽኦ እናበረክታለን"- አባገዳዎች
.
.
በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ አስተያየታቸውን ለኢቢሲ የሰጡት የጉጂ አባገዳዎች ገልጸዋል፡፡

መንግስት በሀገሪቱ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲጠናከር ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ ኦነግን ጨምሮ ባርካታ የፖለቲካ ድርጅቶች ወደ ሀገር በመግባት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ በኦሮሚያ በአንዳንድ አካባቢዎች ከሰላማዊ መንገዱ ውጭ በሚደረግ እንቅስቃሴ ከሰው ህይወት አልፎ፣ በአካል በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

አባገዳዎች እንዳሉት ሰሞኑን በኦሮሚያ የሰላም ሳምንት መታወጁን ተከትሎ የታጠቁ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ሰላማዊ ትግል ተቀላቅለዋል፡፡

የኦሮሞ አባገዳዎች ለየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ሳይወግኑ በኦሮሚያም ሆነ በአገሪቱ ሳላማዊ ፖለቲካ ትግል ብቻ ባህል እንዲሆን የጀመሩትን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) ከኦነግም ሆነ ከሌሎች ተፎካካሪ ፖለቲካ ድርጅቶች ያለውን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት እንዳለበትም አባገዳዎች አሳስበዋል፡፡

ኢቢሲ እንደ ዘገበው በኦሮሚያ በተለያዩ ስፍራዎች እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶች በህብረተሰቡ የእለት ተዕለት እንቅስቃሴዎች ላይ እክል መፍጠራቸውንም አባገዳዎች ጠቁመዋል፡፡

ሁሉም አባገዳዎች በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላም እንዲፍን የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

እስካሁን ድረስ #አስተማማኝ የሆነና #ዘላቂ መፍትሄ ያልተገኘለት የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ዳግም ሌላ የከፋ እልቂት እንዳያስከትል ከፍተኛ ስጋትን ደቅኗል።

ከጥቂት ወራት በፊት ተደርሶ የነበረው ለሰብዓዊነት ግጭት የማቆም ውሳኔ መላ ህዝብ በተስፋ ሲጠብቅ የነበረውን ጥቂት የሰላም ጭላንጭል አሁን እየታየ ያለው የዳግም ጦርነትና ግጭት ሁኔታ የታየውን ተስፋ እንዳያጨልመው ስጋት ደቅኗል።

በእርግጥ ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ ተብሎ በታወጀበት ወቅት እንኳን በየአቅጣጫው ያሉትና ለዚህ ወገን እንወግናለን የሚሉ ሚዲያዎች ፣ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲከኞች የጦርነት እና ግጭት ቅስቀሳዎች፣ ጥላቻንና የሰዎችን አእምሮ ለዳግም ጦርነት የማዘጋጀት ድርጊትና እቅስቀሳ አላቆሙም ነበር።

እስካሁን ባለው ጊዜ አቀራራቢ እና ሰላም ላይ ትኩረት ያደረጉ ስራዎች በአግባቡ አልተሰሩም ፤ ግጭት ቆመ ይባል እንጂ በተለይ በሚዲያ የሚሰራው ስራ ሰዎች ከጦርነት ስነልቦና እንዳይወጡ የሚያደርግ ነበር።

በተለያዩ አካላት እየተሞከሩ ነው ስለሚባሉት የሰላም ጥረቶች መላው ህዝብ ይሄ ነው የሚባል ዝርዝር መረጃ የለውም ፤ ይህንን ጥረት የሚያደርጉ አካላትም ለስራው እንቅፋት እንዳይሆነ መረጃውን ለመስጠት ባለመፈለጋቸው ከኃላ ለሰላም እና ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ስለሚደረገው ጥረት እና እንቅፋት ስለሆኑ ጉዳዮች በትክክል ማወቅም አልተቻለም።

ከሰሞኑ ግን ከፍተኛ የጦርነት ዝግጅቶችና ቅስቀሳዎች ፣ የሚዲያ ዘመቻዎች ከየአቅጣጫው ተጧጡፈው በመቀጠለቸው ለሰላም የነበረውን ተስፋ ዳግም እያደበዘዘው ይገኛል።

ሌላው በትግራይ ክልል ላለው በብዙ ሚሊዮን እርዳታ ጠባቂ ግጭት የማቆም ውሳኔ ከተደረሰ በኃላ በየቀኑ መግባት የነበረበት 100 ተሽከርካሪ ለምን እየገባ እንዳልሆነ ለዚህ ደግሞ ማን ? ምን ? እንቅፋት እንደሆነ በግልፅ የሚያብራራ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አድራጊ ድርጅትም ብቅ አላለም።

የሆነው ሆኖ ግን አሁን ላይ በየአቅጣጫው የሚታየው የግጭት እና የጦርነት ቅስቀሳ ፣ ጥላቻን የመዝራት ዘመቻ ዳግም የከፋ እልቂት እንዳይመጣ የሚያሰጋ ሲሆን፤ ከግጭት እና ጦርነት ቀጠና ራቅ ያሉ አካላት ገና ከወዲሁ በሁኔታው የዩትዩብ ገንዘብ መሰብሰቢያ ፣ የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ ማድረግ ጀምረዋል።

ከዚህ በፊት በነበረ ጦርነት ሳቢያ እጅግ የተዳከመው ኢኮኖሚ፤ አሁን በሩስያና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት በዓለም ያለው ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚያዊ መናጋት በሀገር ውስጥ ዳግም ጦርነት ተደርጎ ኢኮኖሚው እንዳያንሰራራ ሆኖ እንዳይወድቅ ያስፈራል ፤ ይህ ደግሞ ይዞት የሚመጣው መዘዝ እጅግ የከፋ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA " ለኢትዮጵያ አንድነት ፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቁርጠኛ ነን " - አሜሪካ አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ማይክ ሀመር ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር #ውጤታማ ውይይት አድርገዋል ስትል አሳወቀች። ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ አዲስ…
አምባሳደር ማይክ ሐመር ምን አሉ ?

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በኢትዮጵያ ከነበራቸው የ10 ቀናት ቆይታ በኃላ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የተለያዩ ሃሳቦችን አንስተዋል።

ኤርትራን በተመለከተ ፦

" የኤርትራ ሠራዊት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ ለጦርነት መሰለፉ ያሳስበናል፤ እንቃወማለንም። የትኛውም የውጭ ተዋናይ የኢትዮጵያን የግዛት ሉዓላዊነት ማክበር ጦርነቱ እንዳይቀጣጠል ያግዛል። ስለዚህ ጉዳይም #ከአስመራ ጋር ቀጥታ የምንወያይ ነው የሚሆነው። ጦርነቱ በኢትዮጵያ የትግራዋይ፣ አማራ እና አፋር ህዝብን ሰቆቃ ያበዛል። ይባስ ብሎ የኤርትራ ሠራዊት በዚህ ላይ መሳተፍ ሌላኛውን አስከፊ ሁኔታ እንዳያስከትል እንሰጋለን። "

የጦርነቱን ዘላቂ መፍትሄ በተመለከተ ፦

" የጦርነቱን #ዘላቂ የሆነ መፍትሄ መምጣት ያለበት ከኢትዮጵያውያን ከራቸው ነው። ሀገራቸው እኮ ነው። በዚህ ውስጥ የዩናይትድ ስቴትስ ሚና ይህን ከባድ ጊዜ እንዲያልፉ በጠንካራ ዲፕሎማሲ ማገዝ ነው። ተስፋ የምናደርገውም ተፋላሚ ኃይላቱ ከአውዳሚ ጦርነት ወጥተው ተስፋና ብልጽግና ወደ ሚያመጣው ሰላም ይመጣሉ የሚለውን ነው። "

ማዕቀብን በተመለከተ ፦

" ቀዳሚው ትኩረታችን ዲፕሎማሲ ነው። ተፋላሚዎቹ ወደ ሰላም እንዲመጡ አሜሪካ የተለያዩ አማራጮችን ትመለከታለች፤ ለጊዜው ግን ዋነኛው ትኩረታችን በዲፕሎማሲ አብዝተን መስራት ነው። እንደ የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ህብረት ያሉ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጋር እየሠራን ያለነውም ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ነው። "

መተማመንን በተመለከተ ፦

" የተፋላሚዎች ቁልፍ ልዩነት እርስ በርስ መተማመም አለመዳበር ነው። ተፋላሚዎችን ወደ አንድ ለማምጣት ዋናውና መሰረታዊው ጉዳይ መተማመንን በሂደት መገንባት ነው። በጦርነቱ በተሰቃየው ህዝብ መካከልም ይህን የመተማመን ስሜት ማስረጽ ያስፈልጋል። ያን መተማመን የሚያመጡ ሂደቶችት ላይ ነን አሁን። "

የኢትዮጵያን አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነትን በተመለከተ ፦

" አሜሪካ የኢትዮጵያን አንድነት፣ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ታከብራለች፤ ኢትዮጵያውያንን ሚጠቅም ዘላቂ ሰላም እንዲኖር ነው የምትሻው "

ያንብቡ : https://telegra.ph/USA-09-20-2
#ኢትዮጵያ

በፕሪቶሪያ የተፈረመው #የሰላም_ስምምነት ለዘላቂ ሰላም አስተዋፅኦ ያደርጋል ? ወይስ አያደርግም ? በሚሉት ነጥቦች ክርክር እና ውይይት እንዲደረግ ከ #USAID በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ " ሀበጋር " (የደበበ ኃ/ገብርኤል የህግ ክርክር ፕሮግራም) ባለፈው ቅዳሜ አንድ የውይይት እና ክርክር መድረክ ተዘጋጅቶ ነበር።

በመድረኩ ላይ የተጋበዙ ምሁራን ፣ የሕግና የፖለቲካ ባለሙያዎች ፣ የፖለቲካ ፖርቲዎች በየፊናቸው ሀሳብ ሲሰጡ ፤ የተለያዩ ጥያቄዎችንም ሲሰነዝሩ ተስተውለዋል።

የታሪክ ምሁር እና የቀድም #የአብን ብሔራዊ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም (ዶ/ር) የፕሪቶሪያው ስምምነት " #ዘላቂ ሰላምን አያመጣም " በማለት፣ እንዲሁም የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አበበ ገ/ህይወት " ስምምነቱ ዘላቂ ሰላም ያመጣል " በማለት ክርክር አድርገዋል።

በአንድ ወገን ያሉት ተሳታፊዎች ስምምነቱ ከነችግሩም ቢሆን ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ በሌላ ወገን ደግሞ ስምምነቱ አሳታፊና ግልፅኝት፣ ተጠያቂነት መርሆችን ካላሟላ ዘላቂ የሆነ ሰላም ሊመያመጣ አይችልም ፣ ቀድሞውንም አሳታፊነት እና ግልጸኝነት የጎደለው ነው በማለት ሀሳባቸውን አቅርበዋል።

በመድረኩ ፦

- የፕሪቶሪያው ስምምነት ዘላቂ ሰላም ያመጣል ? አያመጣም ?
- የተፈናቃዮች ጉዳይ
- የራያ እና ወልቃይት ጉዳይ ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ክርክርና ውይይት መድረኩ የተሳተፉ አካላትም አነጋግሯል።

ያንብቡ - https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-19