TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አርባ ምንጭ! ነገ በአርባ ምንጭ ከተማ በአዲስ አበባ ዙሪያ የተፈፀመው ድርጊት የሚያወግዝ ሰልፍ እንደሚደረገ ሰምቻለሁ። ጨዋው የአርባ ምንጭ ህዝብ ተቃውሞውን እና ሀዘኑን በሰላማዊ መልኩ እንደሚገልፅ ሙሉ እምነት አለኝ። ለዚህ ደግሞ ሰላም ወዳዶቹ የአርባ ምንጭ ወጣቶች ምስክር ናቸው።
.
.
ተጨማሪ...

የጋሞ ጎፋ ዞን አስተዳደር ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ለጊዜው የ1 ሚሊየን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ የተጠቆመ ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ የተፈፀመውን ድርጊት በእጅጉ ኮንኗል። ጋሞ ጎፋ ዞን ብሔር ብሔረሰቦች ተቻችለው #በፍቅር የሚኖርበት ዞን በመሆኑ መላው የዞኑ ህዝብ በትግስት እና #አኩሪ ዕሴቱን በመጠበቅ እንዲሁም በህግ #ተቀባይነት የሌለው ተግባር #በላመፈጸም እንዲተባበር ከዞኑ ጥሪ ቀርቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን⬆️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን #በስራ እንቅስቃሴዎቻቸው ጎልተው በመውጣት ከተጠርጣሪዎች #የገንዘብ መደለያ #አንቀበልም ሲሉ ለህግ በማቅረብ ለሰሩት #አኩሪ ተግባር ለአመራርና ለአባላቱ የገንዘብ ሽልማት ሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia