TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቭላድሚር_ፑቲን

የሩስያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ሩስያ ከአፍሪካ ጋር ላላት ግንኙነት ቅድሚያ እንደምትሰጥ ተናገሩ።

ይህን ያሉት ትናንት ሰኞ ሞስኮ ውስጥ መካሄድ በጀመረውና ከ40 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን እየተካፈሉበት እንዳሆነ በተነገረው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ነው።

ፕሬዜዳንት ፑቲን ምን አሉ ?

" አገራችን ከአፍሪካ አገራት ጋር ለመተባበር ቅድሚያ እንደምትሰጥ እና በዚህም እንደምትቀጥል አጽንኦት መስጠት እፈልጋለሁ።

ከዩክሬን በሚቀርበው እህል ላይ የተደረሰው ስምምነት ካልታደሰ ሩሲያ ለተቸገሩ የአፍሪካ አገራት #በነጻ እህል ታቀርባለች።

በባለፉት ዓመታት ሲላክ የነበረውን የእህል መጠን ለአፍሪካ አገራት በተለይም ከሩሲያ ለሚፈልጉ በነጻ ለማቅረብ ዝግጁ ነን።

ሩሲያ የደረሰችባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለአፍሪካ አገራት ታካፍላለች ፤ የኤሌክትሪክ ሀይል እንዲያመርቱ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች።

አፍሪካ እያቆጠቆጠ ባለው የብዝኃ የዓለም ስርዓት ላይ ስልጣኗን እና ሚናዋን ማሳደግ እንደምትቀጥል አምናለሁ። "

#BBC

@tikvahethiopia