TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢህአዴግ‼️ በየአካባቢው አየተስተዋለ ያለው #መፈናቀልና ሰብዓዊ መብት #ጥሰት በምንም መልኩ ኢህአዴግ እንደማይታገስ ተመለከተ። ለዚህም #የፀጥታ_አካላት ተገቢውን #እርምጃ እንዲወስዱ አቅጣጫ ተቀምጧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አንድነት ለፍትህና ዴሞክራሲ ፓርቲ፦

#ኢትዮጵያዊነትን የሚፈታተኑ #ችግሮችን ለመከላከል ህዝቡ ለአንድነቱ ፀንቶ መታገል እንዳለበት አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አሳሰበ፡፡

ከዘረኝነትና ከማንነት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ #ግጭቶችን በአገራችን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የዜጎች #መፈናቀልና ሞት መፈጠሩ አሳስቦኛል ያለው ፓርቲው መንግስት ከሰብዓዊ መብትና ከፀጥታ ጋር ተያይዘው ያሉ ህጎች ባአስቸኳይ ሊያስፈፅም ይገባል ብሏል።

በሃገሪቱ እዚህም እዚያም ያሉ #ግጭቶችን የሚፈጥሩ ግለሰቦችንም ሆነ ፖለቲከኞች የመለየት ስራ የህዝቦችም ሃላፊነት ነው ያለው ፓርቲው በየትኛውም አካል ጥፋት ህዝቡ መጎዳት እንደሌለበት ገልጿል።

መንግስት #ህጎችን በማስከበር ዜጎች በፈለጉት ክልል በነፃነት የመኖርና የመንቀሳቀስ መብታቸውን የማስከበር ህገ መንግስታዊ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ተገልጿል።

ምንጭ፦ ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia