TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት⬆️

"ዛሬ #በሰመራ ከተማ ቀጠና 4 ተብሎ በሚስጠራው አካባቢ የሀገር #መከላከያ 6ኛ ሜካናይዝ ክፍለጦር አባላት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 30 ተማሪዎች ለአዲሱ አመት የደብተር እና የእስክርቢቶ ስጦታ አብርክተዋል። ለሁሉም ተማሪዎች ከ1-12 ክፍል እንደየደረጃቸው ነው ስጦታው የተበረከተላቸው። H.E.A ከሰመራ"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እውነታው ይሄ ነው‼️

"ኢትዮጲያ ዉስጥ በግልፅ ንገረን ካላችሁ፦ የመጨረሻ ኢትዮጲያ የምትባል ሀገር ያለችዉ #መከላከያ ዉስጥ ነዉ። ሌላዉማ ስለቀበሌዉ እና ስለቤተሰቡ #የሚያላዝን ህዝብ ነዉ ያለዉ ኢትዮጲያ ዉስጥ። ባለቤት ያጣች አሳዛኝ ሀገር ናት ኢትዮጲያ። ሁሉም #ስለመንደሩ የሚያወራ÷ ሀገር የሚባል ነገር ባለቤት ያጣባት #አሳዛኝ ሀገር ናት ኢትዮጲያ። ኢትዮጲያ ካለች÷ አሁን መከላከያ ዉስጥ ነዉ ያለችዉ። ወደዚ ዞር ስትሉ 'አካም' ትላላችሁ÷ ወደዚ ዞር ስትሉ 'ሰላም' ትላላችሁ÷ ወደዛ ስትዞሩ በሌላ ቋንቋ ትግባባላችሁ። ሌላ ቦታማ የለም÷ 'ዉጣልኝ እኮ ነዉ ያለዉ' እየያችሁ አይደለም?የኔ ካልሆንክ ዞር በል ነዉ ሌላ ቦታ ያለዉ። 'ኢትዮጲያዊ ነህ #ይገባሀል ኑር የሚል አይደለም። "

▪️ክቡር ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ▪️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️

#ሼር #Share

በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለምትገኙ በሙሉ -- የተከሰተውን #ግጭት ለማርገብ እና ሰላም ለማስከበር የመከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ይሰራል።

አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ #የተከለከሉ ተግባራት፦

• ከጎንደር - መተማ መስመር 5 ኪ.ሜ. ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ #በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሳሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• "ሰላም ለማስከበር" በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፍቃድ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

#ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል #እርምጃ ይወሰድበታል‼️

የሰላም ጥሪ፦

የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ሀይሉ ጋር እንድትሰሩ #መከላከያ_ሰራዊት ጥሪ አቅርቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️

#ሼር #Share

በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለምትገኙ በሙሉ -- የተከሰተውን #ግጭት ለማርገብ እና ሰላም ለማስከበር የመከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ይሰራል።

አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ #የተከለከሉ ተግባራት፦

• ከጎንደር - መተማ መስመር 5 ኪ.ሜ. ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ #በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሳሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• "ሰላም ለማስከበር" በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፍቃድ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

#ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል #እርምጃ ይወሰድበታል‼️

የሰላም ጥሪ፦

የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ሀይሉ ጋር እንድትሰሩ #መከላከያ_ሰራዊት ጥሪ አቅርቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከባቲ- ከሚሴ በአንድ ግለሰብ ሲዘዋወር የነበረ 880 የክላሽ ጥይት ኮምቦልቻ ከተማ ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር ያለለት ዘገዬ ለአብመድ እንደተናሩት ዛሬ ሚያዚያ 2 ቀን 2011 ዓ.ም ረፋድ ላይ 880 የክላሽ ጥይቶችንና 400 ሺህ ብር የያዘ የባንክ ደብተር ይዞ ሲጓዝ የነበረ ግለሰብ መናኸሪያ ባሉ ተራ አስከባሪዎች እና የትራንስፖርት ባለሙያዎች ተይዞ ለፖሊስ መሰጠቱን አስታውቀዋል፡፡

አንዳንድ የመረጃ ምንጮች ደግሞ ግለሰቡ 8 ሺ 150 ብር በካሽ፣ የሞባይል ካርድና ፓስፖርት ይዞ መገኘቱን ተናግረዋል::

በአካባቢው ሰላም የሚያውኩ ድርጊቶች እንዳይፈጠሩ የክልሉ ልዩ ኃይል፣ ፀረ ሽምቅ፣ ሚሊሻ እና የአካባቢው ፖሊስ ተሰማርቶ እየጠበቀ እንደሆነም ኮማንደር ያለለት ተናግረዋል፡፡ ወደ አካባቢው የሀገር መካለከያ ሠራዊት እንደገባም ለአብመድ አስታውቀዋል፡፡

አካባቢው #ትልልቅ ድርጅቶች የሚገኙበት በመሆኑም ጥቃት እንዳይደርስባቸው ከወጣቱ እና ከአካባቢው ማኅረሰብ ጋር በመተባበር ጥብቅ ጥበቃ እየተደረገላቸው እንደሆነ ነግረውናል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ ኮማንደሩ አስታውቀዋል፤ ኮምቦልቻ እና አካባቢዋ ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ባይኖርም #ስጋት ለመቅረፍ #መከላከያ በአካባቢው መኖሩን ኮማንደሩ አመልክተዋል፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መከላከያ_ሰራዊት በቤንች ማጂ ዞን ተዘግተው የቆዩ መንገዶችን እንዲከፈቱ አድርጓል። #ኢትዮጵያ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #መተከል አካባቢ ለሚገኙ የሀገራችን ዜጎች‼️ #ኢትዮጵያ #ETHIOPIA #ቤንሻንጉል

#መከላከያ_ሰራዊት
#ፌደራል_ፖሊስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መከላከያ_ሰራዊት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጽንፈኛ ሀይሎችንና ህገ-ወጦችን በመታገል የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አስታወቀ፡፡ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታና በሰራዊቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደዋል፡፡ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በሰራዊቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ አተኩሮ የተካሄደውን ውይይት ያስጀመሩት የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አደም መሀመድ ናቸው፡፡ ከፍተኛ አመራሮቹ በቅርቡ በተቋሙና በአማራ ክልል አመራሮች ላይ የደረሰው አደጋ ታላቅ ቁጭት መፍጠሩን በመግለጽ በቀጣይ ድርጊቱ እንዳይደገም እንደሚሰሩ በውይይቱ ማጠቃለያ ባወጡት ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ አረጋግጠዋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱና ለህዝቦች ሰላም መስዕዋትነት እየከፈለ የመጣ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው በቀጣይም የተለያዮ #ጽንፈኛ ሀይሎችንና ህገ-ወጦችን በመታገል የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አስታውቋል፡፡ ሰራዊቱ ከምንጊዜም በላይ ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት ለመወጣት በሚያስችለው ቁመና ላይ እንደሚገኝና የተሰውት ጓዶች ህልፈት አባላቱን ለበለጠ #ጀግንነትና መስዋዕትነት የሚያነሳሳ እንጂ #የሚያዳክም እንዳልሆነ ገልጿል፡፡

ምንጭ፦ የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክቶሬት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ2013 ምርጫ ሂደት ሊያስተጓጉል ይችላል ?

የምርጫ ቁሳቁስ ማጓጓዣ ችግር አፋጣኝ እልባት ካላገኘ አገር አቀፉን የምርጫ ሂደት ሊያስተጓጉል ይችላል ሲል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ።

የኢትዮጰያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ያሳወቀው በመራጮች ምዝገባ መረጃ፣ በምርጫ ቁሳቁስ ስርጭትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ከተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ጋር በተወያየበት ወቅት ነው።

የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ሰፊ አገርና ህዝብ ነገር ግን የመንገድ መሰረት ልማት ውስንነት ያለበት አገር ላይ ምርጫን በአግባቡ ለማካሄድ መንግስት ከፍተኛ እገዛ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

ሁሉንም የአገሪቱ አካባቢ ሊሸፍን የሚችል የትራንስፖርት አቅም ያለው #መከላከያ_ሰራዊት መሆኑን የገለጹት ሰብሳቢዋ በትግራይ በነበረው ሁኔታ በተፈጠረው ጫና እገዛው መስተጓጎሉን ተናግረዋል።

ያለው የማጓጓዣ ችግር አፋጣኝ እልባት ካልተሰጠው የምርጫ ሂደቱን በከፍተኛ ሁኔታ ሊያስተጓጉል ይችላል በማለት ተናግረዋል ሰብሳቢዋ።

ምርጫ ቦርድ በመላ አገሪቷ 663 የምርጫ ክልሎችን ከፍቶ የምርጫ ቁሳቁሶችን እያጓጓዘ ሲሆን በቀጣይ ለ50 ሺህ ምርጫ ጣቢያዎች እንደሚያሰራጭ አስታውቋል።

ማጓጓዣው በየአካባቢው እንዳለው መሰረተ ልማት በየብስ ፣ በጀልባ እንዲሁም በበቅሎና ፈረስ ጭምር ሊሆን እንደሚችል ነው ያመለከቱት።

ለዚህም ደግሞ በየደረጃው ያሉ የክልል አመራሮች የመጓጓዣ ችግሩን ለመፍታት ከቦርዱ ጋር መተባበር እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት። (ENA)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጄነራሉ ምን አሉ ?

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምክትል ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ እና ለመከላከያ ሰራዊት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ቃለመጠይቅ ሰጥተዋል።

ይኸው ቃለመጠይቃቸው ዛሬ ለህዝብ ተሰራጭቷል።

ጄነራሉ ምን አሉ ? በተለይም ስለ ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ጉዳይ ምን ሃሳቦችን አንስተው ተናገሩ ?

ጄነራል አበባው ታደሰ ፦

- መላ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቅልን የምንፈልገው በሀገሪቱ የፀጥታ ኃይል እንዲገነባ ህገመንግስቱ የሚፈቅደው #መከላከያ_ሰራዊትና #ፌዴራል_ፖሊስን ነው።

- በየክልሉ ያለው ልዩ ኃይል በሳይዙ ልክ አለው ፤ በሌላ አነጋገር ሀገር በሚመስል ደረጃ 14 እና 15 ሬንጀር አለው ይሄ ፈፅሞ አይቻልም።

- አሁን ያለው የክልል ልዩ ኃይልን መልሶ የማደራጀት ስራ ዛሬ የተጀመረ / በሞራል የተገባበት ሳይሆን ከዚህ ቀደም ለረጅም ጊዜ ጥናት ተደርጎበት ነው።

- የክልል ልዩ ኃይሎች ፦ የክልልን ፀጥታን ይጠብቁ ነበር ፣ ከእኛ (ከመከላከያ) ጋር ሆነው ይሞቱ ነበር ህይወታቸውን አሳልፈዋል ፣ ቆስለዋል ደምተዋል። ይሄ ኃይል ይሄን የመሰለ ትልቅ ኳሊቲ ነበረው።

- ከህገመንግስት አንፃር ስናየው እነዚህ ኃይሎች ህጋዊ አይደሉም ህገመንግስቱ እውቅና አይሰጣቸውም። ለክልል ኃይል የሚሰጠው መደበኛ ፖሊስን ብቻ ነው። ህገመንግስቱ የታጠቀ ኃይል የሚያውቀው አንደኛ መከላከያ፣ ሁለተኛ ፌዴራል ፖሊስ፣ ሶስተኛ መደበኛ ፖሊስ ነው ከዚህ ውጭ ህገመንግስቱ አይልም።

- የኃይል አገነባቡ (የልዩ ኃይል መዋቅር) ብሔር ተኮር ነው ፤ ለኦሮሞ ህዝብ እሞታለሁ ብሎ ቃል ይገባል አማራውስ ? ጉዳዩ አይደለም ማለት ነው በግልፅ አማርኛ ፤ አማራው ደግሞ ይመጣና ለአማራ ህዝብ እሞታለሁ ይላል ኦሮሞውስ ? ጉዳዩ አይደለም ። ብሄር ተኮር ስለሆነ ሀገር አቀፍ የሆነውን አብሮነት የመኖር ፤ የህዝቦችን አንድነት ይሸረሽረዋል።

- የክልል ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ፕሮግራም ወደ መከላከያ ሰራዊት ማስገባት፣ ወደ ፌዴራል ፖሊስ ማስገባት፣ ወደ መደበኛ ፖሊስ ማስገባት ነው። በማን በራሱ ምርጫ፣ በምን ? ክብሩን ሞራሉን ፣ ጥቅሙን በማይነካ ሁኔታ።

- አፈፃፀሙ በተመለከተ ሁሉንም እኩል እደራጀዋለን ፣ በጥንቃቄም ይሰራል።

- አንደኛውን ክልል ኃይል እንዲኖረው ሌላውን ክልል ኃይል እንዳይኖረው አናድረግም። ይሄ ኢትዮጵያ ውስጥ አይታሰብም።

- የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ለምሳሌ የትግራይ የትግራይ ክልል እንደማንኛውም ክልል መደበኛ ፖሊስ ብቻ ነው የሚኖረው ፣ የታጠቀ ልዩ ኃይል የሚባል በፍፁም አይኖረውም።

- በአንዳንድ የአማራ ክልል አካባቢና ዩኒቶች ካልሆነ በስተቀር አማራ ልዩ ኃይል የሚባለው በአብዛኛው ተቀብሎታል ፤ ይሄ በኮሚኒኬሽን ያለ ችግር ነው ይሄን የኮሚኒኬሽን ችግር እየፈታን ነው ያለነው። አፈፃፀሙ ላይ የታየው ጉድለት ይሄ ነው እንዲህ አይነት ነገር ሊኖር እንደሚችል እንጠብቃለን አስበንም ነው የገባነው። ከዛ  ውጭ ባወጣነው ፕሮግራም መሰረት ይሄን ኃይል ወደምንለው ፕሮግራም እናስገባዋለን ሁሉንም እኩል አድርገን።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-04-07
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ?

ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱና የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን እንዲከበር ጠይቀዋል።

በጥቅሉ ያነሷቸው ጥያቄዎች  ምንድናቸው ?

- የመከላከያ አባላት የነበሩት ጨምሮ ሌሎች የፓለቲካ እስረኞች ይፈቱ፤
- የትግራይ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት የወሰዱት የብድር ወለድና ቅጣት ይነሳ፤
- የመንግስት ሰራተኞችና የጡረተኞች ውዙፍ ደመወዝና አበል ይከፈል፤
- ከትግራይ ሰራዊት (TDF) ለተሰናበቱ ታጣቃዊች ማቋቋምያ ይከፈል፤
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ይከበር፤
- ከረሃብ ጋር በተያያዘ እርዳታ ይደረግ ፤
- የህወሓት የህጋዊነት ጥያቄ ለምን ዘገየ ?
የሚሉና ሌሎች ይገኙባቸዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምን መለሱ ?

ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ብዙ ስኬቶች እንዳሉ አሁንም ግን የሚቀር ብዙ እንዳለ ገልጸዋል። ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በጥይት ሰው እንዳልሞተ ተናግረዋል። በትግራይ መረጋጋት ፤ መንግሥት መመስረት ፣ ህወሓት (TPLF) ከሽብርተኝነት መፋቅ የስምምነቱ ውጤት ነው ብለዋል።

ከስምምነቱ በኃላ በርካታ ቢሊዮን ብሮች በካሽም በቁሳቁስም ወደ ትግራይ ክልል መላኩን ገልጸዋል።

እስረኞችን መፍታት በተመለከተ ፦

" ስብሃትን ፈትቼው የለም እንዴ ? ፣ አልፈልግም እንዲታሰሩ።

የመከላከያን በተመለከተ እራሱ ይነግራችኋል (ዶ/ር አብርሃምን ማለታቸው ነው) አላውቅም በእኔ እውቀት #አንድም_የታሰረ_ሰው_የለም።  ከስራ ያቆምናቸው ታጋዮች ነበሩ እርቁ ሲፈፀም መፍታት እኮ አይደለም ወደቦታቸው ነው የመለስናቸው። አሃዱ አለቃ ናቸው ሁሉም በየቦታው በየደረጃው ኃላፊዎች ናቸው መከላከያ ውስጥ ...

እስረኛ በሌብነት ምክንያት ካለ አላውቅም ፤ እስረኛ ሰው ገድሎ የታሰረ ወንጀለኛ ካለ አላውቅም። ከግጭቱ ጋር የሚያያዝ ግን በመከላከያ ወጥተው የነበሩት ተመልሰው መከላከያ ውስጥ ገብተዋል።

እኛ እንደዚህ አይነት ፍላጎት የለንም። የምናውቀውም የለም። እኛ እስረኛ ፈተን ስራ አስፈፃሚ ፈተን ጌታቸው ጋር የቀሩ እስረኞች ነበሩ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያልፈታቸው ። "

ትግራዋይ ተፈናቃዮችን በሚመለከት ፤ ተፈናቃዮች በስምምነቱ መሰረት ቤታቸው መመለስ አለባቸው ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የአማራ ክልሉ አቶ አረጋ ፣ ዶ/ር አብርሃም ያሉበት ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰሞኑን ንግግር ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል።

የፌዴራል መንግሥት ፍላጎት መጀመሪያ የተፈናቀሉ ሰዎች በሙሉ ቤታቸው እንዲመለሱ ነው ያሉ ሲሆን " በማንኛውም ሰዓት ነገ ሁመራ ያለው ቤቴ መመለስ እፈልጋለሁ የሚል ካለ እኛ ለመመለስ ዝግጁ ነን " ብለዋል።

#መከላከያ በአካባቢው የትግራይም ይሁን የአማራ ፀጥታ ኃይል እንዳይኖር ኃላፊነት እንደተሰጠው ገልጸዋል።

ሁሉም ሰዎች ወደ ቤታቸው #ከተመለሱ_በኃላ እራሱ ህዝቡ አስተዳዳሪውን እንዲመርጥ እንደሚደረግና ከተረጋጋ በኃላ ህዝቡ ሪፈረንደም በማድረግ " እኔ አማራ ነኝ ፤ እኔ ትግራይ ነኝ " የሚለውን እንደሚወስን ተናግረዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ተፈናቃዮች መቐለ ፣ ሽረ መቀመጥ እንደማያስፈልጋቸውና ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። በዚህ ረገድ ፌዴራል መንግሥት የሚጠበቅበትን እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በነበረው ሁኔታ ውጭ ሀገር የሄደ ባለሃብት ካለ መመለስ ይችላል ፣ ከባላሃብቶች ጋር በተያያዘ ችግር ካለም ይፈታል ብለዋል።

#ረሃብን በተመለከተ ጉዳዩን ፖለቲካዊ ማድረግ እንደማይገባና ትግራይ ተርባ ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል በልቶ ጠግቦ እንደማያድርግ ገልጸዋል። " ጌታቸውንም ወቅሼዋለሁ ረሃብ ካለ መደወል ነው እኔ ጋር ያለ አምጡ አግዙ ማለት ነው ቀላል ነው በትዊተር ከሆነ ግን እኛ በትዊተር አንነጋገርም ብሄዋለሁ ለሌሎች ነው የነገርከው እንጂ እኔ አልሰማሁም " ሲሉ ገልጸዋል። " ረሃብ ረሃብ ችግር ችግር አለ የሚል ፖለቲካ " ማድረግ ተገቢ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኮሚቴ ተቋቁሟል ሄዶ ጥናት አድርጎ መደረግ ያለበት ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል።

የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/TPLF እውቅናን በተመለከተ ጉዳዩ የምርጫ ቦርድ ቢሆንም " በእኛ በኩል መሰጠት አለበት ብለን እናምናል ፤ በቅርብም #አነጋግረናቸዋል የሚፈታ ይመስለኛል ፤ ብዙም ከባድ አይደለም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

#ከባንክ ጋር በተያየዝ ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን በማስረዳት መናገር ያልፈለጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሯቸው አማካሪዎች እና ጉዳዩን በቀጥታ የሚያዩ የሚመለከታቸው አካላት ተነጋገረው የሚቻል ነገር ካመጡ ለማገዝ ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመዋል።

ከባንክ ብድር ጋር በተያያዘ " ብድር ተከለከልን " የሚሉ ባላሃብቶች ካሉ ከዶ/ር አብርሃም እና ከሌሎች የሚመደቡ ሰዎች ጋር እንዲነጋገሩ አቅጣጫ ሰጥተው አልፈዋል። በመንግሥት ፖሊሲ ሊፈታ የሚችል ካለ ግን እንደሚታይ ገልጸዋል።

በኤርታራ መንግሥት (በሻዕብያ ኃይል) ስለተያዙ መሬቶች በተመለከተ ፤  የፌዴራል እና ከትግራይ የጋራ ኮሚቴ መቋቋሙን በዚህም የሀገር መከላከያ ከትግራይ ጓዶች ጋር በመሆን ቦታዎችን እንዲያዩ እንደሚደረግ ገልጸዋል። " #ከአልጀርስ_ስምምነት ውጭ የሆነ ካለ ሪፖርቱ ሲመጣ እናያለን ፤ ማንም የማንንም ቦታ በኃይል ይዞ ለዘላለም መኖር አይችልም እንዳንዋጋ፣ ዳግም ግጭት እንዳይፈጠር ትርፍ ነገር የተካሄደ ካለ አይተን ቦታውን ለይተን ኦፊሻሊ እነዚህ ነገሮች ይስተካከሉ ብለን በንግግር መልክ ልናበጅ እንችላለልን " ብለዋል። ውጤቱ ታይቶ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል ሲሉ ተግረዋል።

➡️ የጡረተኞችን ውዝፍ ክፍያን በተመለከተ ምንም ሳይሉ አልፈው በአቶ ጌታቸው በኩል ያለውን ነገር እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።

ሌሎችም አንዳንድ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ በቀጥታ አስተያየት ባይሰጡም በጥቅሉ በክልሉ ካሉ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በውይይት በምክክር እንደሚፈቱ ቃል ገብተዋል።

#TikvahFamilyMekelle
#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia