TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን #በአፍሪካ_ህብረት የመሪዎች ስብሰባ የውሃ ችግር እንዳይከሰት ልዩ ኮማንድ ፖስት አቋቁሞ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ መሪዎቹ ስብሰባ የሚያካሂዱበትን አካባቢ ጨምሮ ያርፉባቸዋል ተብለው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለዩ 56 ሆቴሎች ውሃ በአግባቡ እንዲደርስ እየሰራ መሆኑን፥ የባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት መሪ ወይዘሮ #ሰርካለም_ጌታቸው ተናግረዋል።

ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው ይህ ስራም ከአቃቂ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ውጭ በሁሉም ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች የሆቴሎቹን ዝርዝር በመበተን ከጥር 15 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

በዚህ ሂደትም ሆቴሎቹ ውሃ የሚያገኙበትን መስመር የመፈተሽና ሲቋረጥ ያላቸውን የውሃ መጠን በመለየት በቦቴ ተሽከርካሪ ማቅረብ የሚያስችል ስራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ከጥር 29 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ በማዕከል የሚመራ ኮማንድ ፖስት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ እየሰራ ይገኛልም ነው ያሉት።

ኮማንድ ፖስቱ ሆቴሎቹ በሚገኙባቸው መገናኛ፣ መካኒሳ፣ አራዳ እና ንፋስ ስልክ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመንቀሳቀስ የሚያግዝ ባጅ በመያዝ እየሰራ ይገኛል።

ልዩ ኮማንድ ፖስቱ በዋናነት በስብሰባው ወቅት ለመሪዎቹ የውሃ አገልግሎት እንዳይቋረጥና በዚህ ሳቢያ የሃገሪቱ ገጽታ እንዳይበላሽ ለማድረግ የሚሰራ ነው።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
AU🔝

#በአፍሪካ_ህብረት በሚካሄደው የ32ኛው የመሪዎች ስብሰባ ላይ የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ መታሰቢያ ሀውልት ዛሬ የካቲት 03 ቀን 2011.ዓ.ም በይፋ #ተመርቋል፡፡ በቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በህብረቱ ግቢ ውስጥ የቆመላቸው ሀውልት #ከነሃስ የተሰራ ነው፡፡

Via ETV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ እንገናኝ!
(TIKVAH-ETHIOPIA)

ነገ #StopHateSpeech እንቅስቃሴ በሀዋሳ ዩንቨርስቲ ይካሄዳል። ውድ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አካላት ነገ ቻናላችን #በአፍሪካ_ህብረት_አዳራሽ ባዘጋጀነው ልዩ ዝግጅት ላይ እንድትገኙ ጋብዘናችኃል። የሀገራችን ጉዳይ የሚያሳስባችሁ፤ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቀቃማችን መታረም አለበት የምትሉ፤ ፍቅር በሀገራችን እንዲስፋፋ እንፈልጋለን የምትሉ፤ ጥላቻ ክፉ ነው የምትሉ፤ ሰላም ከሁሉም ነገር ይቀድማል የምትሉ፤ ለሌሎች የሀገሪቱ ወጣቶች አርአያ እንሆናለን የምትሉ ሁሉ በአዳራሹ እንገናኝ!! የክብር እንግዶች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ይገኛሉ።

ነገ ቅዳሜ ምሽት 12:00 ሌላ ቀጠሮ እንዳትይዙ! ከሀገራቹ፤ ከፍቅር የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።


ፍቅርን እንዝራ!!
ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#በአፍሪካ_ህብረት_አዳራሽ ከምሽት 12:00 ጀምሮ እንገናኝ!! መላው የሀዋሳ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች!! #StopHateSpeech
አንድ ብር ለወገኔ የበጎ አድራጎት ማህበር ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበርና ከብሄራዊ አደጋ ስጋት መከላከል ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከፊታችን ግንቦት 23_25 ድረስ የሚቆይ የደም ልገሳ ፕሮግራም እንዲሁም ቅዳሜ ግንቦት 24 በአይነቱ ለየት ያለ ፕሮግራም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ተዘጋጅቶ እርሶን እየጠበቆት ነወ።
በዕለቱ ታላላቅ ሰዎች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህም መካከል
1⃣ የአነቃቂ ንግግር (motivational speech) አቅራቢ የሆኑት #ዶክተር_በድሉ_ዋቅጅራ
2⃣ የተለያዩ ገጣሚያን እና ደራሲያን እንዲሁም የተለያዩ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የሚገኙ ክለባት ስራቸውን ያቀርባሉ።
ሰለሆነም #ተማሪዎች _ለሰብአዊነት በሚል መሪ ቃል በሚዘጋጀው በዚህ ልዩ ፕሮግራም ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የፕሮግራሙ መቅረቢያ ቦታ #በአፍሪካ_ህብረት
የመግቢያ ዋጋ 2.00 birr
VIP 5.00 birr
@OBFMC
@OBFMC
@OBFMC
ለበለጠ መረጃ +251904451280
+251965818419
+251973156161
TIKVAH-ETHIOPIA
#UpdateAU የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ዛሬ ተቀብለው ማነጋገራቸውን በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አሳውቀዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም #በአፍሪካ_ኅብረት_የሚመራውን የሰላም ሂደት ዓለም አቀፍ አጋሮች እንዲደግፉ መስማማታቸውን…
#ETHIOPIA

ዛሬ እና ባለፉት ቀናት ምን ሆነ ?

- የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ከፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረዋል በተጨማሪ ከህወሓት መሪ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋርም በምን አይነት መልኩ  እንደተነጋገሩ ባይታወቅም ተነጋግረዋል (እንደ አሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ)። ሐመር ዛሬም እዚሁ አዲስ አበባ ናቸው።

- አምባሳደር ሐመር ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ እና ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ጋር ተወያይተዋል።

- የአፍሪካ ህብረት በኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ላይ " ሙሉ እምነት " እንዳለው ገልጾ ኃላፊነታቸውን አራዝሟል።

- ኦባሳንጆ እና ሙሳ ፋኪ ተገናኝተው ተነጋግረዋል።

- ዛሬ  በአዲሱ ዓመት ደግሞ ከዚህ ቀደም በኦባሳንጆ ላይ እምነት የለኝም ያለው ህወሓት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ከፌዴራል መንግስት ጋር እደራደራለሁኝ ሲል መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ፦

በአፍሪካ ኅብረት የሚመራ ተዓማኒ የሰላም ሒደት እንጠብቃለን ብሏል።

• በ " አፍሪካ ህብረት መሪነት " ለመደራደር ዝግጁ ነኝ ፤ ለድርድሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፣ ለአፋጣኝ እና በሁለቱም ወገኖች ስምምነት ተግባራዊ ለሚደረግ የተኩስ አቁም ዝግጁ ነኝ ብሏል።

• በ2ቱ ወገኖች ተቀባይነት የሚኖራቸው አደራዳሪዎች ፣ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች እና ዓለም አቀፍ ባለሞያዎች በሰላም ሂደቱ ሊሳተፉ ይገባል ብሏል።

• ተደራዳሪዎቹ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳይ እንደሆኑ ገልጾ በፍጥነት ተደራዳሪዎቹን ለመላክ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

• ለዚህ አሳዛኝ ግጭት ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ማምጣት የምንችለው #በሰላማዊ_ውይይት_ብቻ እንደሆነ እርግጠኞች ነን ብሏል።

➣ ዛሬ በ "ህወሓት" በኩል በወጣው መግለጫ ላይ ቅድመ ሁኔታዎች ተብለው የተዘረዘሩ ነጥቦች የሉም።

የ " ህወሓት " ን የዛሬ መግለጫ በተመለከተ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ መንግስት የተባለ ነገር የለም። ነገር ግን ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ መሆኑን በማረጋገጥ ፤ የሰላም ድርድር ኮሚቴውን አባላት በዝርዝር ማሳወቁ አይዘነጋም።

የሰላም ሂደቱ ተፈፃሚ የሚሆነው #በአፍሪካ_ህብረት ጥላ ስር ብቻ እና ብቻ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለፁ ይታወሳል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ መንግስት ህወሓት ዳግም ጥቃት መክፈቱን ካሳወቀ በኃላም በተደጋጋሚ ባወጣቸው መግለጫዎች ለሰላም የዘረጋው እጅ እንዳልታጠፈና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ " ህወሓት " ወደ ተከፈተው የሰላም በር እንዲመለስ ግፊት እንዲያደርግ ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#UNGA

የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረውን ግጭት #በአፍሪካ_ህብረት አማካኝነት በሚደረግ የሰላም ድርድር ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለፁ።

አቶ ደመቀ ፤ ይህንን የገለፁት በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው 77ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።

አቶ ደመቀ መኮንን ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተፈጠረውን ግጭት በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት በሚደረግ የሰላም ድርድር ለመፍታት ቁርጠኛ ነው ያሉ ሲሆን " ከአፍሪካ ሕብረት ውጭ የሚደረግ ሌላ አካሄድ ተቀባይነት አይኖረውም። " ሲሉ ተናገረዋል።

በሌላ በኩል በንግግራቸው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ #በአፍሪካ_ህብረት ማዕቀፍ ስር በሚደረግ የሶስትዮሽ ድርድር ጉልህ ተፅዕኖ በማያደርስ እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መርህን መሰረት በማድረግ ልዩነቶችን ለመፍታት አሁንም ፅኑ አቋም አላት ሲሉ ለጉባኤው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በንግግራቸው አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት ውስጥ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ጠይቀዋል።

" እኛ አፍሪካውያን ይህ ጥያቄያችን ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ ይህን ጥያቄ መጠየቃችንን እንቀጥላለን። " ብለዋል።

ምትክል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን የሚችለው ፤ የሚሰጠውም ጭምር በፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ተገቢው ውክልና ሲኖራት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ደመቀ መኮንን ዛሬ ምሽት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጉባኤ ላይ ያሰሙት ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል (40 MB)።

@tikvahethiopia